እነሆ ጄኔራሉ እንዲህ ይሉናል፣
#1-: ከ27 አመት በኃላ ብአዴን እና እነ አባዱላ ገመዳ የትግራይ የበላይነት አለ ብለው ሲያነሱ በጣም አፍርባቸዋለሁ። ድሮ እነ አባዱላ ይሄን ለማንሳት ይፈሩ ነበር ማለት ነው?
( እኔ: ብአዴን እና አባዱላ ትፈሩ ነበር እንዴ?)
#2 -: ” ኢፍትሐዊነት” በስፋት ያለው በራሳቸው በክልሎች ውስጥ ( ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን) እንጂ በክልሎች መካከል አይደለም።
( እኔ: ሚስተር ጄኔራል የኦህዴድ እና ብአዴን ድርጅታዊ መግለጫ አልተመለከቱትም እንዴ? ወይስ አይስማሙበትም?)
#3 -: ኢህአዴግ የፓሊሲ ችግር የለበትም። ችግሩ ማስፈፀም አለመቻል ነው።
( እኔ:- ሚስተር ጄኔራል #3 እና ቀጥሎ የሚፃፈውን #4 ንግግርዎን ለማዛመድ ይሞክሩ።)
#4 -: ትግራይ ውስጥ ግብርና መር ፓሊሲ አይሰራም።
( እኔ:- ሚስተር ጄኔራል ታዲያ ሌላው ምን ተዳው ነው?)
#5 -: ፋብሪካ የተከማቸው አዲስ አበባ ላይ ብቻ ነው። እዚም እዚያም ያለው ፋብሪካ ጥቂት ነው። ዋናው ግን የፋብሪካ መብዛት ሳይሆን የአእምሮ ልማትና የአስተሳሰብ እድገት ነው።
( የጋዜጠኛ አንሙቴ ኢንቴግሪቲ:- አንሙቴ መጀመሪያ ” ሰው እኮ ፋብሪካ እየቆጠረ ነው” በማለት ህዝቡ የአእምሮ ልማት አለማሰቡን አጣጥሎ ሳይጨርስ የተናገረውን ረስቶት ” እኔ ግን ጋንቤላ ውስጥ አንድ ፋብሪካ አለመኖሩ ቅር ያሰኘኛል” ይለናል።
( እኔ:- አንሙቴ ኢንቴግሪቲውን ለጊዜው ትቼው ቅሬታህን ግን እኔም እጋራለሁ። እርግጥ የጋንቤላን መሬት 70 በመቶው የተቀራመቱት የትግራይ ተወላጆች መሆናቸው ስጨምርበት ደግሞ ቅሬታዬ የትየለሌ ይሆናል።)
#6 :- ተቃዋሚዎች የመከላከያ ሰራዊታችን ጄኔራሎች ትግራይ ነፃ አውጪ ናቸው ይላሉ። አሁንም እንደዛ ያስባሉ። ይሄ ትክክል አይደለም። የመከላከያ ሰራዊታችን በአሁን ሰአት ተመጣጥኗል።
( እኔ:- ሚስተር ጄኔራል እስቲ ጄኔራሎቹን በብሔረሰብና በያዙት የስልጣን ቦታ ዘርዝረው ያቅርቡልን? አደራዎትን የኮማንድ ፓስቱ የህዝብ ግንኙነት ሐላፊ ጄኔራል መሐመድ ፣ ብሔረሰብ አማራ ብለው እንዳያሸማቅቁን! አንሙቴም ቢሆን እዝች ጋር ያሳየሃትን ከኢንተግሪቲ መንሸራተት ሌላ ሰው ሳያያት አርማት)
#7 :- ሕውሓት ጠንካራ ድርጅት ነበር። አሁን ግን እንደዛ አይደለም።
( እኔ: – No comment!)