“ጉራጌ ሌብነት እንጂ ፖለቲካን የት ያውቃል እየተባልኩ ምራቅ እየተተፋብኝ ነበር ስደበደብ ነው የከረምኩት “
“ከደበደቡኝ ሰዎች መሀል የአሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለሰ አለም አንዱ ናቸው” ሰይፉ አለሙ ተሰማ
(በጌታቸው ሽፈራው)
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2018/03/by-Getachew-Shiferaw-21032018-300x247.jpg)
መዝገቡ የሚጠራው በእነ ጌታሁን በየነ ሲሆን ለዛሬ የተቀጠረው ተከሳሽ ሰይፉ አለሙ የመከላከያ ምስክሮቹን ለማሰማት ነው ተከሳሽም የተከሳሽነት ቃሉን ሰጥቶል።
*በማዕከላዊ ከመርማሪዎች ጋር ሳይሆን ጥቃትን ከሚያደርሱ አካላት ጋር ነበርኩ።
* እኔ የተያዝኩት አርባምንጭ ሆቴል ውስጥ ነው የያዘኝም ደህንነት ነው ይዞም ማዕከላዊ የሚባል ሲኦል ውስጥ ነው የከተተኝ የተረከበኝም ኮማንደር ተክላይ ነው
*ይደበድቡኝ የነበሩት በጣም ብዙ ናቸው ሴቶችም አሉበት ከኮማንደር ተክላይ ጋር ሰክረው ነበር የሚደበድቡኝ
*ከሚደበድቡኝ ሰዎች መሀከል የአሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ መለሰ አለም አንዱ ነበር
*በማዕከላዊ ጥቃት ይደርስብኝ የነበረው በቤሄሬ ነው ጉራጌ ሌብነት እንጂ ፖለቲካን የት ያውቃል እየተባልኩ ምራቅ እየተተፋብኝ ነበር ስደበደብ የነበረው
*ከዚህ በፊትም ማዕከላዊ ተይዘው የገቡ ብዙ ጉራጌዎች ተደብድበዎል ተኮላሽተዎል በዚህ ቤሄር ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ሊቆም ይገባል
*ሰውነቴ ላይ የሚታዩት እነዚህ ጠባሳዎች ከእናቴ ማህፀን ስወለድ ያገኘሆቸው ሳይሆኑ በማዕከላዊ በደረሰብኝ ድብደባ ምክንያት ሰውነቴ ላይ የቀሩ ናቸው
*ይሄ ሁሉ ድብደባ ደርሶብኝ ሰውነቴም መግሎብኝ ህክምና እንኮን አለገኘሁም ነበር
*በጊዜው አብረውኝ የነበሩ እስረኞች ህክምና ያግኝ ብለው የረሀብ አድማ አድርገው ነበር ሀላፊዎቹም ህክምና ይደረግለተል ብለው ቃል ከገቡ በሆላ እኔን ጠርተው አንተን አናክምህም ብለው ማስታገሻ ብቻ ሰተውኛል
*ስደበደብ የነበረውም የግንቦት ሰባት አመራር ነህ ተብዬ ነው
ሲል የተከሳሽነት ቃሉን የሰጠ ሲሆን ሶስተ የመከላከያ ምስክሮች አቅርቦ አሰምቶል
*ምስክሮቹም በወቅቱ መዕከላዊ አብረው መታሰራቸውን ገልፀው ሰይፉ አለሙ ላይ ይደርስ የነበረውን ሰቃይ በድብደባ ምክንያት ሰውነቱ ላይ ይታዩ የነበሩ ቁስሎችን እና የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ የረሀብ አድማ ማድረጋቸውን ገልፀው ለፍ/ቤቱ አስረድተዎል
ፍ/ቤቱም በመከላከያ ምስክሮች ላይ ብይን ለመስጠት ለሚያዚያ 16/2010 ዓ.ም ቀጠሮ ሰቶል
—‘-””””