>

እኛ የኤደን ባህረ ሰላጤ አሽዋዎች (በ አሸናፊ በሪሁን)

እኛ የኤደን ባህረ ሰላጤ አሽዋዎች

 በ አሸናፊ በሪሁን

የመንን እና ሶማሊያ የሚለየው የኤደን ባህረ ሰላጤ የአለማችን ትልቁ የባህር ላይ የንግድ መስመር ነው፡፡ በእስያ እና የ አውሮፓ ሀገራት ትልቁ የንግድ መገናኛም ይህ መስመር ነው፡፡ ይህ የንግድ መገናኛ መስመር ታዲያ ህገ ወጥ ሰው አዋዘዋሪዎች ስደተኞችን ውደ አረብ ሃ እና ወደ አውሮፓ ሀገራት ለማሻገር የሚጠቀሙበት ዋነኛ መስመር ነው፡፡  ክፋቱ ታዲያ ከዚህ ትልቅ ኤደን የባህረ ሰላጤ አካባቢ የሚወጡ ዜናዎች ግሁሌም ሞትን የሚያበስሩ መሆናቸው ነው ፡፡ ከሞች ስደተኞች መካከል ደግሞ በርካታውን ቁጥር የሚይዙት የእኛው ዜጎች ኢትዮጵያውያን መሆናቸው የበለጠ ሀዘንን ያጭራል፣ አንገትንም ያስደፋል፡፡ ከዚህ በፊት በነሀሴ 2009 ዓ.ም በየመን አድርገው ወደ ሌሎች አገሮች ለመሄድ በነበረ ጉዞ 160 ኢትዮጵያዊያን ወደ የመን ባህረ ሰላጤ ተወርውረው አሽዋ ሆነው ቀርተዋል፡፡ ይህ  ዜናም ለመላው ኢትዮጵያውያን በተለይ ደግሞ ለሞች ወላጆቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው አሳዛኝ እና አስደንጋጭ ነበር ።ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በግንቦት 2010 ዓ.ም ሌላ አሳዝኝ ዜና ሰምተናል፡፡ 100 ስደተኞችን ይዛ ስትጎዝ የነበረች ጀልባ በመስመጦ የ46 ኢትዮጵያውያን ህይዎት አልፎል፡፡ የተለያዩ መስመሮች በመጠቀም ከኢትዮጵያ ወደ ተቀረው_ዓለም_የሚደረግ_ህገ_ወጥ_ስደት_የብዙ ኢትዮጵያውያንን ህይዎት መቅጠፉን እንደቀጠለ ነው፡፡ በቅርቡ እንደሰማነውም 57 ኢትዮጵያውን ይህን መስመር ተጠቅመው ለማለፍ ሲሞክሩ ባጋጠማቸው አደጋ ህይዎታቸውን አጥተዋል ፡፡

በየመን _በሚካሄደዉ_የርስበርስ ጦርነት_ሳቢያ_የደረሰዉ_ሰብዓዊ_ቀዉስ እነዚህን_ስደተኞች_በህገ_ወጥ ሰው አዘዋዋሪወች እጅ እንዲወድቁ እያደረጋቸዉ_ ነዉ። እንደ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ዘገባ  ለስደተኞችን ክፍት በተተወ ድንበር ህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ስደተኞችን እንደ ልብ እያስገቡበት በመሆኑ ዛሬም በወር 7,000 የሚሆኑ ስደተኞች ይህንን አደገኛ የባህር ላይ ጉዞ በመጋፈጥ በየመን አቆርጠው ለማለፍ ይሞክራሉ፡፡ እስከ ሞት የሚያደርስ አደጋ እያጋጠማቸዉም ቢሆንም ባለፈዉ_ዓመት_ብቻ_ ወደ 87 ሺህ የሚጠጉ ሰደተኞች የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ባህር አቋርጠዉ ወደ የመን ጉዞ አድርገዋል።በዚህ_ጉዞም_በርካቶች_የኤደን ባህረ ስላጤ አሽዋ ሆነው ቀርተዋል ፡፡  በባለፈው የጎርጎሮሳዊው 2018 ዓም ብቻ በሜዴትራንያን ባህር አድርገው የአውሮፓ ህብረት ደቡባዊ ድንበር ወደ ሆኑት ጣልያን፣ ግሪክ ፣ማልታ እና ስፔን የገቡ ስደተኞች ቁጥር ከ 112 ሺህ በላይ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ዘገባ ያስታውሳል ። ሌሎች ከ6700 በላይ ስደተኞች ደግሞ_በእግር ስፔን ገብተዋል። እነዚህ ከአደገኛ የበረሃ እና የባህር ጉዞ አሽዋ ሳይበላቸው እንደ ዕድል በህይወት ተርፈው አውሮፓ መድረስ የቻሉት ብቻ ናቸው። በአንጻሩ መንገድ ላይ የባህር አሽዋ ሲሳይ ሆነው የቀሩትን ቤት ይቁጠራቸው።የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን  በዚህ የጉዞ መስመር የሞቱ እና የደረሱበት ያልተወቀ ስደተኞች ቁጥር 2262 በላይ መሆኑን አስታውቋል። ታዲያ ይህን እየሰሙና እያዩ አሁንም ሰዎች በህገ- ወጥ መንገድ ይሄዳሉ። የስደተኞች ስቃይና መከራም በዚያው ልክ ቀጥሎል።ምክንያቱም የሚደረገው በህገ ወጥ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ እነዚህ ስደተኞች ገና እግራቸው ከቤት ከመውጣቱ በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎችና ደላሎች እጅ ውስጥ ይገባሉ፡:፡ ከዚያም በእነዚህ ሰብአዊነት የማይሰማቸው ሰዎች ከፍተኛ የሆነ ስቃይና መከራ እንዲያሳልፉ ይገደዳሉ። ሲከፋም ህወታቸውን እስከመንጠቅ ይደርሳሉ።

በአብዛኛው ወጣት የሆኑ ስደተኞች በአደገኛ ጉዞ ከኢትዮጵያ ለመሰደድ ከሚያበቋቸው ምክንያቶች ውስጥ በውጭ ዓለም ሥራ እና ገንዘብ በቀላሉ ይገኛል የሚሉ የተጋነኑ እና በቀቢፀ – ተስፋ የተሞሉ መረጃዎች ናቸው ፡፡ወጣቶችም እንዲህ አይናቸው እያየ እና ጀሮቸው እየሰማ ስደትን ያውም በህገ ወጥ መንገድ የሚመርጡበት ምክንያት በደንብ ሊፈትሹት ይገባል ፡፡ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ማሳለፍ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚሁ ባሻገር ማህበረሰቡም ቢሆን ይን ህገ ወጥ ስደት ሊያሳስበው ይገባል፡፡  በየበረሃው ለሰዎችና ለዱር አውሬዎች ሲሳይ እና ያለ ነጋሪና ቀባሪ እየቀሩት ያሉት ስደተኞች ከአብራክኩ የወጡ ልጆቹ ናቸውና። የሀገር ውስጥ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑት ተቅዋማትም ጉዳዩን አተኩረው ሊሰሩበት ይገባል። በዚህ ጉዳይ ላይ መንግስትን እና ማህበረሰቡን በማማከርም ዜጎች ዘላቂ ኑሮአቸው በሚሻሻልበት እና የተሻሉ የስራ አማራጮች መፍጠር ላይ ሊሰሩ ይገባል። የሁሉም ባለድርሻዎችና የሚመለከታቸው አካላት ትብብርና ርብርብ ችግሩን በመፍታት ሂደት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ፡፡ መንግስት ይህን የዜጎችን እንግልትና ችግር በመመልከት ዜጎች ለስራ ወደ ውጭ ሲጓዙ የሚያጋጥማቸውን ሞት፣ እንግልትና ስቃይ ለመታደግ  ህጋዊ የአሰራር ማዕቀፍን አበጅቷል። አዋጅ ቁጥር 923/2008 የውጭ ሀገር የስራ ስምሪትን ህገዊ በሆነ መንገድ ለመፈፀም የተዘጋጀ ነው። በዚህ አዋጅ ተመርቶ በህዊ መንገድ ወደ ውጭ የስራ ስምሪት ማድረግ ራስን ከአደጋ ቤተሰብን ደግሞ ከሃሳብና ከሰቀቀን ይታደጋል፡፡ ይህን አዋጅ የህገ ወጥ ደላላዎችን መንገድ ለመዝጋት የሚያግዝ ነው ። ይሁን እንጀ ለህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መፍትሔው በመንግስት አዋጅ ላይ ብቻ የተጣለ አይደለም፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን ጎን ክልሎች ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት የራሳቸውን ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ህዝቡ በየቀየው ስደተኞችን ወደ ሞት የሚገፉ ህገ ወጥ አዘዋዋሪዎችን እነማን እንደሆኑ ያውቃል። በመሆኑም ስራቸውን በመቃወም አሳልፎ በመስጠት የልጆቹን ህይዎት ለመታደግ መጣር ይኖርበታል ፡፡  በየክልሉም ስለ ህገወጥ ስደት እና አደጋዎቹ ግንዛቤ የመፍጠር መጠነ ሰፊ ስራ ከተሰራ ችግሩን መቅረፍ ይቻላል። ታዋቂው ሙዚቀኛ ቴዎድሮስ ካሳሁን ( ቴዲ አፍሮ ) ኩርኩማ አፍሪካ በሚለው ዜማው ላይ ፡-

ከእንግዲህ ይብቃ ስቃይ በምድርሽ ላይ

ሄዶ ከመሆን የባዳ አገር ሲሳይ …………

እንዳለው እኛ ኢትዮጵውያንን  ባህር ላይ የአሽዋ ሲሳይ ከመሆንን ይብቃ ማለት ይኖርብናል፡፡ ታዋቂው ገጣሚ በዕውቀቱ ስዩም “እኛ “በሚል ግጥሙ ላይ የእኛ የኢትዮፕያውያንን የስደት ስቃይ እንዲህ ሲል አስፍሮታል፡፡

ኖረን እኮ አናውቅም

ከባህር ጠርዝ ላይ

እንደ ክቡር ድንጋይ

እሬሳ ስንለቅም።

ከሙሴ ተምረን

ባህር መግመስ ሲያምረን

በታንኳ ሄድንና በሳጥን ተመለስን…….

በቅርቡን 32ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ላይ መሪዎቹ ስደትን ለመከላከል እና ተመላሽ ስደተኞችን ለማቆቆም የሚረዱ ስትራቴጀዎችን በመንደፍ እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል ፡፡ ሁሉም ህገ ወጥ ስደትን ለመከላከል በርትቶ ከሰራ  ከስደት ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያውያን የሞት ዜና የማንሰማበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም እላለው፡፡ ያኔም እኛ ኢትዮጵያውያን የአውሬ ሲሳይ እና የበርሀ አሽዋ ከመሆን እንተርፋለን ፡፡

       (አሸናፊ በሪሁን seefar በተሰኘ መንግስታዊ ባልሆነ ተቆም ውስጥ የሚዲያ ባለሙያ ናቸው)

Filed in: Amharic