
የእቴጌ መነን አሥፋው ታሪክ ምን ይመሥላል? በአገዛዙ ላይ ምን አይነት ሚና ነበራቸው?

በፍቃዱ ጌታቸው
ግርማዊ እቴጌ መነን መጋቢት 25 ቀን 1883 ዓም በወሎ ጠ/ግዛት በአምባሰል አውራጃ ልዩ ስሙ ዕጏ ከተባለው ቀበሌ ከጃንጥራር አስፋውና ከወ/ሮ ስሀን ሚከኤል ተወለዱ። እቴጌ መነን በልጅነት ዘመናቸው በእናት በእባታው ቤት ሀህምሀር ተቀጥሮላቸው እማ ርኛ ማንበብና መፃፍ ጠንቅቀው አወቁ። በተጏዳኝ ልዩ ልዩ የቤ ት ባልትና ሙያዎችን ተምረው በማጠናቀቃቸው የቤት ራስ ለመባል በቅተዋል፡፡
በ1892 ማለትም በተወለዱ በአሥረኛ እመታቸው ለመጀመሪያ ባለቤታቸው በህግ ተዳሩ፡፡ ከእኝህ ባለቤታቸው ወ/ሮ በላይነሽ ዓሊንና ጃንጥራር አስፋው ዓሊን ወለዱ፡፡ ከዚያም ሁለተኛ ባለቤታቸውን በማግባት ጃንጥራር ገብረእግዚ አብሄር አመዴንና ወ/ሮ ደስታ እመዴን ወልደዋል፡፡ በ1903 ዓም ወደ መጀመሪያ ራስ ልኡልሰገድ እጥናፍሰገድን አገቡ። በዚሁ ዓመት ወደ መጨረሻም ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጋር ተጋቡ። የእቴጌ መነን እና የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጋብቻ ፓለቲካዊ ሢሆን የአጎታቸ ውን የልጅ ኢያሡንና የቀዳማዊ ኃይለሥላሤን ጠብ ለማስወገድ ይቻላል በሚል መኳንንቱ ሁሉ በተለይም እነራስ ቢትወደድ ተስማ ናደው መክረው የፈፀሙት ነበር፡፡
እቴጌ መነን ከቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ያፈሯቸው ልጆች ስድስት ሲሆኑ ዝርዝራቸውም የሚከተለው ነው
ልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሤ
ለዑል አልጋወራሽ እስፋወሠን ኃይለሥላሴ
ልዕልት ዘነበወርቅ ኃይለሥላሤ
ልዕልት ፀሃይ ኃይለሥላሤ
ልዑል መኮንን ኃይለሥላሤ
ልዑል ሣህለሥላሤ ኃይለሥላሤ

የጣሊያን ወራሪ ኃይል ኢትዮጵያን እንደሚወር ይፋ በሆነበት ጊዜ ግርማዊት እቴጌ መነን መስከረም 1 ፤ ቀን 1928 ዓ፡ም፡ የዘመን መለወጫ ዕለት ለዓለም ሁሉ ሴቶች የትግል ጥሪ አድርገው ነበር፡፡ በንግግራቸውም “በዓለም ያላችሁ ሴቶች ሁሉ በዓለም ላይ እውነተኛ ፍርድና ሰላም እንዲነግስ የመንግሥት ስዎ ች ሁሉ በሚሠሩት ሥራ በእግዚአብሔር መንፈስ እንዲመሩ በምና ደርገው ፀሎት ተባባሪዎች እንድትሆኑ እንለምናለን” የሚል ነው።
እቴጌ መነን በ1928 ዓ፡ም፡ ግርማዊ ባለቤታቸው ጦር ሜዳ ሄደው ከጠላት ጋራ ስላገራቸው ሢዋጉ በከተማው ያሉ ወይዛዝርትን እየ ሰበሰቡ ለቁስለኞች እና ለሠራዊቱ የሚሆን ስንቅ፣ ትጥቅና የህክም ና ቁሳቁስ እያዘጋጁ ይልኩ ነበር፡፡ የከተማውም ፀጥታ እንዲጠ በቅ ከከተማው የዘበኛ ኃላፊዎች ጋር በመመካከር በትጋትና በብር ታት ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ በጦር ሜዳ ካሉት ለባለቤታቸው እና በዚያው ከሚገኙ የመረጃ ሰዎች የጣሊያን አውሮፕላኖች በአዲስ አበባ በሚኖረው በሰላማዊ ህዝብ ላይ የቦንብ ጥቃት ለማድረስና ህፃን፣ ሽማግሌና ሴት ሳይለይ በአንድነት ለመደምስስ እየመጡ እንደሆነ በስልክ በተላለፈ ጊዜ ግርማዊት እቴጌ መነን በአውቶ ቢል ሆነው በድፍረት በከተማው እየዞሩ በየመንገዱና በየገብያው ያለው ህዝብ በአንድነት እጅብ ብሎ መቆሙን ትቶ እንዲበተንና እደ ጋውን ወደሚከላከልበት ቦታ አንዲደበቅ በማድረጋቸው ብዙ ህዝብ ሊድ ን ችልሏል፡፡
እቴጌ መነን በፓለቲካዊ አስተሳሰብ የተነሣ የእና ታቸው የወሮ ስህን ወገኖች በተለይም እያታቸው ንጉሥ ሚካ ኤልና አጉታቸው ልጅ ኢያሱ ከባለቤታቸው ከቀዳማዊ ኃይለሥላ ሴ ጋር በፈጠሩት ፓለቲካዊ ቅራኔ ሰበብ በተካሄደው የሰገሌ ጦር ነት ከግራ ከቀኝ ተሰልፈው የተዋጉ ወገኖቻቸው ያለቁባቸው ቢሆ ንም በየጊዜው ሁለቱንም ወገኖች እያስማሙ በአንድነት እንዲኖሩ አስችላዋል፡፡ ይህንን የእቴጌ መነን አለፋውን ብርታት በማስታወስ አርብ የካቲት 9 ቀን 1954 ዓ፡ም፡ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋ ቸው በተቀበሩ በበነጋው ባለቤታቸው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ቀጥሎ ያለውን ንግግር አድርገው ነበር፡፡
“ሁላችሁም ከምታውቁት በላይ እኛ አራሣችን በቅርቡ የምናቃት ልንገልጠው የሚገባን ክፉ ቀን የማይለውጣት፣ ሃይማኖተኛ፣ በደጉም ጊዜም ዓለማችን ላይ ተጣልተን ሰው አስታርቆን የማያውቅ፣ ሣራ አብርሃምን አንደምትታዘዘው እሷም የእኛን ሃሳባችንን ፈፅማ የእግዚእብሄር ዳኝነት እስኪለየን ድረስ ለህፃናትም ሆነ ለሽማግሌዎች ህዝብም የሚጠቀምበት ጉዳይ ከምትረዳንም በላይ ራስዋ ለማድረግ በምትጣጣረው ባሰራችው ሁሉ ተመስክሮ የተቀመጠ ነው”
የአፄ ኃይለሥላሴ ታሪክ በተባለውና በሌሎችም መፅሃፍት እንደተረጋገጠው እቴጌ መነን አስፋው የአፄ ፋሲል ተወ ላጅ ናቸው፡፡ በዚሁ መፅሃፍ እንደተብራራው ከአፄ ፋሲል ጄምሮ የዘር ሃረጋቸው ሲመዘዝ አያታቸው ንጉሥ ሚካኤል ስምንተኛ ትው ልድ ናቸው፡፡ እናታቸው ወ/ሮ ስሀን ዘጠነኛ እራሣቸው ግር ማዊት እቴጌ መነን አስፋው ደግሞ እስረኛ ትውልድ ናቸው፡፡ በአፄ ፋሲል በኩል እቴጌ መነን እስፋውና ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዝምድና እላቸወ፡፡ዝምድናቸው ግን ጋብቻ የማይከለክል ሲሆን አሥራ ሁለተኛ ትውልዳቸው ላይ የሚገጥም መሆኑን የታሪክ መፅ ሃፍት ያረጋግጣለ፡፡
ግርማዊት እቴጌ መነን አስፋው የካቲት 9 ቀን 1954 ዓ፡ም፡ በተቀበሩበት ዕለት ከተሰሙት የሃዘን እንጉርጉሮ ዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፡፡
የመኮንን እናት ምነው ምን ነካዎ፣
ብቸኛ ጓዶዎን ጥለው መሄድዎ፡፡
እረ ምን ይወራል ምን ትንፋሽ አላና፣
መነን ስታቋርጥ የሞትን ጉዳና፡፡
መኮንን ገሥግሦ ሥላሴ መግባቱ፣
ቤት ሊሠራ ኖሯል ለወላጅ እናቱ።