ሠላም ያገር ሠዉ!! በዛሬዉ ዕለት ህዳር20-2009 ዓ.ም እነ ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ ከታሰሩበት እስር ቤት በሶፍት ወረቀት ተጠቅልሎ የተላከ መልዕክት ነዉ፣ እባካችሁ ለማህበራዊ ድረ-ገጽ ተጠቃሚ ኢትዮጵያዊያንና ለሚመለከታቸዉ ሚዲያዎች በማድረግ የዜግነት ግዴታዎን ይወጡ!!
‹‹ኢህአዴግ ታላቅ ስህተት ላይ ነዉ፡፡ጠላት በማብዛት ድል ያደረገ አንዳች የፖለቲካ ኃይል የለማና!! አሁንም ወጣቶችን በጅምላ በማሰር የሚገኝ መፍትሄ የለም!! የኤዲፐስ መንገድ የፈሩት ሥልጣን ያሳጣል፡፡ወንጀላችን ወጣት ሁነን መገኘታችን ብቻ ነዉ!!አበቃሁ!! ኦሮማይ-ኢህአዴግ!!››
‹‹ሰዉ ፈርቶ የተሻለ ህይወት ሲኖር አላየሁም፤የፍርሃት መንገድ ሁሉ መዳረሻዉ ባርነት ነዉ!!ፈርቶ ከመኖር በድፍረትና በኩራት መሞት የተሸለ ነዉ!!ኢትዮጵያ ለፈሪዎች ቦታ የላትም!!››
‹‹ከዕድገት በህብረት ወደ ‹እስር በህብረት› መራመዳችን እንደ ሀገር እጅጉን አሳዛኝ ክስተት ሆኖ በታሪክ ይመዘገባል!!የማይቀረዉን ለማዘግየት መዉተርተር ትርፉ መላላጥ ነዉ፤የማይቀረዉ አብዮት እንደሆነ ይዘገይ ይሆናል እንጅ አይቀርም!!››