ታምሩ የባድመ ውጊያው ካለቀ በኋላ «በቅነሳ» ሰበብ ከወያኔ ሰራዊት ቢባረርም ያቋረጠውን ትምህት እንደገና ቀጥሎ አስተማሪ በመሆን እስከለተ ሞቱ ድረስ ወሎ ውስጥ ሲያስተምር ቆይቷል። ታምሩ የአገር ዳር ድንበር ትደፈረ ተብሎ በተካፈለበት የባድመ ውጊያ በሻዕብያ ጥይት ሁለት ቦታ ቆስሎ ሕይወቱን ቢያተርፍም፤ ትናንትና ግን አገር ሰላም ብሎ ከቤቱ በወጣበት ከፋሽስት ወያኔ በተተኮሰ ጥይት ተደብድቦ በግፍ ተገድሎ ሳይመለስ ቀረ። ያበሳጫል!
በትግራይ ፖሊሶች በግፍ የወደቀውን ታምሩ በሪሁንን እግዚአብሔር ከቅዱሳን ጋር ከሰማዕታት ተርታ የቆመው ዘንድ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን!