በመከላከያ ኃይል ዉስጥ ዉጥረት ነግሷል
ምክክሩ በአብዘኛው በአማራና እና በኦሮሞ ተወላጆች በተለይም በታችኛው የወታደሩ ክፍል መካከል እነደሆነ ለማወቅ ተችሏል። እያንዳንዱ ንዑስ ወታደራዊ አሓድ በብሔር ተዋፅኦ ላይ ተመስርቶ የተዋቀረ በመሆኑ በሁለቱ ትላልቅ ብሔሮች በኩል እየተነሳ ያለው ጥያቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ሌሎችም ተዛምቶ ሠራዊቱን ወደ መበታታንና ግጭት ሊያስገባ ይችላል ሲሉ ምንጮቼ ስጋታቸዉን ገልፀውልኛል።
ሁልጊዜም የህዝብ አመፅ ሲኖር መከላከያው ውስጥ ውጥረት መፈጠሩ ያለ ቢሆንም የአሁኑ ሁኔታ ግን በፍፁም የልተለመደ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል። ሁሉም የመከላከያው አባላት በሚያምኑዋቸው ሰዎች በኩል በየቀኑ በፖለቲካው አካባቢ እየተካሄደ ያለውን ውጥረት በንቃት እየተከታተሉ እንደሆነ ምንጮቼ ነግረዉኛል።