ከኣስገደ ገብረስላሴ – መቀለ
* የመንግስትና የተፎካካሪ ፓርቲ ፖለቲኮኞች የታማኝ አይነት ኣመለካከትና ቅንነት 10% እንኳን ቢኖሯቸው ሀገራችን ምንኛ ባደገች ነበር ?
እኔ ለኣርቲስት ታማኝ በየነ ኣሜሪካ ለህክምና ሄጀ ሶስት ጊዜ ኢህኣዴግ እንዳያውቅና “ኣሸባሪ ታማኝ በየነ ጋር ተገናኜ” ተብዬ ቅሊንጦ ወስደው ወደ እነ ኣብርሃ ደስታ እንዳይቀላቁሉኝ ፈርቼ በድብቅ ኣግኝቼው ስለሃገራዊ ጉዳይ ተወያይተን ነበር ።
ታማኝ ስለ ኢትዮጵያዊነት ሲተነትን በሆነ መንገድ የኢህኣደግ ኣማራርና የተፎካካሪ ፓርቲዎች የማይተነትኑት ሃሳብ ኣግንቼለት ነበር ።
ዛሬ ግን ሰሞኑን በጎንደርና በባህርዳር በኣደባባዮች በኣዳራሾች ፣ ከመላው የክልሉ ህዝብ ፣ ወጣቶች በቆራጥነት ያለኣንዳች ስጋት በኢህደን ኢህኣደግ ሚዲያ ሲናገረውና ሲያስተላልፈው የሰነበት ስለ ስለኢትየጵያዊነት ፣ ስለኣንድነት በተናገረው ከገመትኩት ካሰብኩት በላይ ረካሁበት ።
በተጨማሪ የታማኝ በዬነ ኣነጋገር በመላው ሀገራችን ላሉት ሙሁራን ተማሪዎች ፣ ወጣቶች ፣ ለእድሜ ባለጸጋዎች ፣ ለኣክቲቪስቶች ያስተማረ ፣ እሩቅ ሄደው ማንነታቸው እንዲመለከቱ ያደረገ እጅግ ቅን ሊሂቅ ዜጋ ኣድርጌ ተቀብዬው ኣለሁ ።
በእኔ እምነት የትግራይ ክልል ባለስልጣናት እንዲፈቀዱለት በትግራይ ክልል ከሁለት በላይ መድረክ ተሰጥቶ መግለጫ ቢሰጥ ለትግራይ ህዝብ ልክ እንደጎንደር መልእክት ቢያስተላልፍ የክልላችን መሪዎች ያለኣንዳች ተጽእኖ ሁኔታው እንዲያማቻቹለት ጥሬን ኣቀርባለሁ ።
ኣርቲስት ታማኝ በየነም ወደ ትግራይ እንድትመጣ ራስህም ግፊት ብታደርግ ። ታማኝ በየነ ሃሳብህን እጅጉን ተመችቶኛል ሁለችንም ከጎንህ ነን ።