ታዋቂው የታሪክ ተመራማሪው ኘሮፌሰር Edward Ullendorff እንዲህ ይላል ” Amde seyon was one of the most outstanding Ethiopian kings of any age and singular figure dominating the horn of Africa ” አምደ ጽዮን በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ የሌለው ጀግና መሪ እንደነበር ሲመሰክር ። ኘሮፌሰር ታደሠ ታምራት ደግሞ “Amdetsion reign is one of the most important formative period in the religious ,Literacy and poletical history ” ሥልጡን የፖለቲካ ፣ የሀይማኖት እና የሥነጽሑፍ ዘዋሪ መሐንዲስ እንደሆነ ይመሠክሩለታል ።
ዓምደ ጽዮን ሲበዛ ጥቃትና በደልን አይችልም… የኢትዮጵያዊነት ደመ ቁጡነት ማሳያ ነው ። ለጦርነት የሚወጣው በደል ገፍቶት እና ከፈጣሪውም ጋር ተማክሮ ነው ። በመጀመሪያ በታቦቱ ፊት ተንበርክኮ ይጸልያል ። የኢየሱስ ክርስቶስ መላእክ ከፊቱ እንደሚቀድም ያምናል ፤ ንግስቲቷና ቀሳውስቱ በመቅደሱ ውስጥ የተስፋይቱ ምድር ለትውልድ ትቀጥል ዘንድ ካለማቋረጥ በጸሎት ይተጋሉ ። አምደ ጽዮንም ለወታደሮቹ እንዲሕ ይላቸዋል “be not Afraid in the face of rebels, for the God of the christians will help us and he will save as from their hands ” Hunting ford page 89