“የአማራ ኢሊቶች..”? (ጌታችው አበራ)

“የአማራ ኢሊቶች..”?

 

    ጌታችው አበራ


የወያኔ ሮሮ፣

የጅል እንጉርጉሮ፣

ሲዘመር ሰምቼ፣

ጆሮዬን አቅንቼ፣

ሳዳምጥ በብርቱ፣

ነበር ለካስ ከንቱ!

 

“ሂሳብ ማወራረድ..

ከአማራ ኢሊቶች”፣

ይል ነበረ ግጥሙ..

የጭካኔው አዝማች፤

ያረመኔ ተግባር ..

ቢሆንም ድርጊቱ፣

መስሎኝ የነበረው..

ሰው ነበር “ኢሊቱ”፤

 

ለካስ በወያኔ፣

በደደቢት ቅኔ፤

ጥማድ በሬዎቹ፣

ላሞች ጥገቶቹ፣

በጎች ፍየሎቹ… 

ነበሩ “ኢሊቶች”..

ያማራ ሃብቶቹ።

 

እንሰሳት ገዳዩ፣

ቡሃቃ አማሳዩ፣

ሆስፒታል ነቃዩ፣

ሬሳ አቃጣዩ…፣

አረመኔ ጨካኝ..

ቦቅቧቃ ማፊያ፣

ወያኔ! ወያኔ!..

የአገር ማፈሪያ!

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.