የኢትዮጵያ ፊደል አባቱን አገኘ !
ማኪ ግርማ

ማንበብና መጻፍ ዋናው ቁምነገር በሆነበት ዘመን ፤ እናትና አባቶቻችን እንኳን መጻሕፍትን ከወዳጅ ዘመድ የተላከውን የናፍቆት ደብዳቤ አንብቦ መልዕክቱን የሚገልጥ ፊደልን የለየ ሰው ማግኘት ከባድ ነበር። ምክንያቱም የአማርኛ ፊደል ማንበብና መጻፍ በቤተክህነትና በቤተመንግሥት ተገድቦ ስለነበር ነው።
ታዲያ ይህ ገደብ ክፍለሃገር ከሚኖሩ ቤተሰባቸው አዲስ አበባ ወደሚኖረው ወንድማቸው የመጡትን የያኔው ታዳጊ ተስፋ ገብረሥላሴንም ጎድቷል። ወደመሐል ሀገር ከመጡ ወዲህ እራሳቸውን ለመለወጥ ሽቶ ከመሸጥ ጀምሮ ያሉ ንግዶችን ሞክረዋል። ፍላጎታቸው ግን መጻሕፍትን መሸጥ ነውና ከተለያዩ ንግዶች ያገኟትን እያስቀመጡ ባጠራቀሙት ጥሪት መጽሐፎችን እየገዙ መሸጥ ጀመሩ።
መቼም ማንበብና መጻፍ እንደህልም የራቃቸውን ማህበረሰብ መጽሐፍ ግዙኝ ማለት ይፈትናል። እንዲያውም አንዳንዶች “አንተን አብረንህ ካልገዛን ማን ያነብልናል” የሚል ምላሽ ይሰጧቸው ነበር። ይህም ለንግዱ እንቅፋት እንደፈጠረባቸው ተረዱና መላውን ይፈልጉ ጀመር። እናም መፍትሔውንም አገኙ።

መጻፋቸው በሀሁ ብቻ አልተገታም። አቡጊዳን ፣ መልዕክተ ዮሐንስን ጨምሮ ከ300 በላይ የሃይማኖት መጻሕፍትን ለማዘጋጀትና ለማሳተም በቁ።
የዚሁ መጻሕፍት አዘጋጅና አሳታሚ ፣ የፊደሉ ገበሬ ታዲያ በዛሬው እለት ታህሣስ ፳፬/፲፰፻፺፭ ዓ.ም ከመምህር ገብረሥላሴ ቢልልኝ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ሥዕለ ሚካኤል ወልደአብ በብሔረ ቡልጋ ነው የተወለዱት።
የእኚህን የዕውቀት በር ፣ ድንቁርናን አጥፊ ታላቅነትና ባለውለታነት መታሰቢያ በማቆም ሲዘክር የተመለከትሁት አንድ ተቋም ብቻ ነው። ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ። አንደኛውን ላይብረሪ በስማቸው ሰይሟል። ሌሎቻችንስ?! ያጎረሰንን እጅ የምንነክሰው እስከመቼ ይሆን???
ነፍስ ኄር!