>
10:49 am - Wednesday March 29, 2023

"በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በ15 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰረት ፍርድ ቤት ውሳኔ አሳልፏል...!!!" (ታሪኩ ደሳለኝ)

“በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በ15 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰረት ፍርድ ቤት ውሳኔ አሳልፏል…!!!”

ታሪኩ ደሳለኝ


*…. ፖሊስ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በመፅሄቱ ላይ ወታደራዊ ምስጢሮችን ጽፏል – ይህን እያጣራሁ ነው በማለት ከጥበቃው ጋር  ክርክር ተካሂዷል።

በዛሬው ዕለት በተሰየመው ችሎት አቃቤ ህግ “አንድ መቶ ሰባት የፍትህ መፃሄቶችን እየመረመርን ነው:: በመፅሄቱ ላይ ወታደራዊ ምስጢሮች ተፅፈዋል:: ተጠርጣሪው የተጠረጠረበት ወንጀል አመፅና ብጥብጥ ለማስነሳት ስለሆነ በፁሁፎቹ ምክኒያት ሞትም ተከስቶ ይሆናል ስለዚህ ይሄንም አጣርተን ክስ ለመመስረት 15 ቀን ፍርድ ቤቱ ይፍቀድልን”

ብለዋል::

ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ በበኩላቸው “እስካሁን ድረስ አቃቤ ህግና ፖሊስ አብረው እየሰሩ ነው የቆዩት:: አቃቤ ህጉም ጉዳዩን ከመጀመሪያ ጀምሮ ያውቀዋል:: ይሄንም ችሎቱ ይረዳል::

ስለዚህ ፍርድ ቤቱ ምንም ተጨማሪ ቀን ሳይፈቅድ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን የተፈቀደለትን የዋስትና መብት አክብሮ ከስር እንዲፈታው እጠይቃለሁ” ብለዋል::

ዳኛው አቃቤ ህግ የጠየቀውን አስራ አምስት ቀን ይሁን በለው ለአቃቤ ህግ 15 ቀኑን ፈቅደዋል::

በመሆኑም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ  ለሰኔ 22/2014ዓ.ም ተቀጥሯል::

[እስካሁን የነበረው ሂደት…]

የፖሊስ ኮሚሽኑ መርማሪ ፖሊሶችን አቃቤ ህጎች

↘️ በመጀመሪያ ጋዜጠኛ ተመስገን ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት በዩትዩቦች ይጠቀማል አሉ፤

↘️ከአስር ቀን ቀጠሮ በኋላ በዩትዩብ ሳይሆን በፍትሕ መፅሔት ይጠቀማል አሉ፤

↘️ፍርድ ቤቱ ይሄን ተከትሎ በዋስ እንዲወጣ ወሰነ፤

↘️ይሄን ተከትሎ የፖሊስ መርማሪዎችና አቃቤ  ህጎች ይግባኝ ብለው ወንጀሉ ውስብስብና ሌሎች አባሬዎች አሉ አሉ፤

↘️ፍርድ ቤቱም ሰኔ 2/2014 በዋለው ችሎት ደግሞ ፖሊስ 8 ቀን ወስዷ ምርምሮ ለሰኔ 10/2014  በድጋሚ ያቅርባቸው ብሎ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ወሰነ::

↘️የሰኔ 10/2014 ቀጥሮ ቀርቶ ዛሬ ሰኔ 7/2014 ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳልኝ ከ5 ቀናት በኋላ ፍርድ ቤት ቀርቦ አቃቤ ህጎቹም የተመስገን ፁሁፍ ወታደራዊ ሚስጥሯች ፅፏል:: ፁሁፍን ተከትሎ ሞትም ተከስቶ ሊሆን ይችላል የሚል አዲስ ክስ አምጥተዋል::

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እስራት፣ በግለሰቡ ብቻ ሳይሆን ሙያው ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው ስንል የሰነበትነው በዚህ ምክንያት ነው።

ቤተሰቦቹ እና የፍትሕ መፅሔት ባልደረቦች

Filed in: Amharic