>

በኦሮሞ ወረራ የጠፉ ብሔሮች! (ጌጥዬ ያለው)

በኦሮሞ ወረራ የጠፉ ብሔሮች!

ጌጥዬ ያለው

ኦሮሞ በ1522 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ከብቶቹን እየነዳ ቶካ ሳር እና ውሃ ወዳለበት አካባቢ ሁሉ በመሄድ በወረራ ነባር የኢትዮጵያ ብሔሮችን አጥፍቷል። በተለይም ሥልጣን ከአንደኛው የገዳ ማህበር መሪ (በእነርሱ አጠራር ሉባ) ወደ ሌላኛው ሲሸጋገር አዳዲስ ወረራወችን መፈፀም ግድ ነው። ካልወረረ፣ ሰዎችን ካልገደለ ሉባ መሆን አይችልም። ጠቅላይ ሚንስትሩ የወራሪው ኦሕዴድ-ብልፅግና ርዕዮተ ዓለም ይሆናል ያለውን የመደመር እሳቤ ከገዳ እንደቀዳው ሲናገር የዘመኑ ሉባ መሆኑን እየነገረን ነው። በመሆኑም እንደማንኛውም የገዳ መሪ መግደል፣ ብልት መቁረጥና መውረር የሥራ ባህሪው ነው። ኦሮምኛ ከሌሎች ቋንቋዎች ተለይቶ በአዲስ አበባ መዘመሩ አፓርታይዳዊነት ቢሆንም አይኑን በጨው ታጥቦ መልካምነቱን በሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ውስጥ ሊነግረን የሞከረውም አዕምሮው በዚህ የገዳ እሳቤ የተቆለፈ ስለሆነ ነው። መከላከያን ገድሏል በማለት በአማራ ላይ ብሔራዊ ጅምላ ጭፍጨፋ እንዲፈፀምበት በምክር ቤት ውስጥ ያደረገው ጥሪም ከዚሁ የሚመነጭ ነው። ብሔር ብሔረሰቦች ተባብረው አማራን እንዲያጠቁ ያደረገው ጥሪም መሪ ነውና ተቀባይነት ሊያገኝ ይችላል። በፓርላማ ውስጥ ነውና የተናገረው ተፈፃሚነቱም ሰፊ ነው። ስለዚህ የአማራ ሕዝብ ራሱን ለማዳን በአንድ ላይ መነሳት አለበት። ከተነሳ ያሸንፋል፤ ጥቃቱ ድመቶች እየፎነጨሩ ዓይኑን ሲያጠፉት፣ ሰውነቱን ሲያቆስሉት እንደ አንበሳ በንቀት መንጎማለሉ ነው።
አማራ ትልቅ ታሪክ ያለው፣ ሰፊ ቁጥር ያለው፣ በመላው ኢትዮጵያ ብሎም በመላው ዓለም የሚኖር፣ በአማራ መስተዳድር ወሰን ውስጥ በአንድ ላይ ተሰባስቦ የሚኖር፣ በተለያዩ ጦርነቶች ጀግንነቱን ያስመከረ ታላቅ ሕዝብ ነው። በመሆኑም ጠላት ቢደራረብ የህልውና ስጋት የለበትም የሚል መከራከሪያ ሊገሳ ይችላል። ሆኖም ይህ ስህተት ነው። ኩርዶች በአመዛኙ ከአማራ የሚመሳሰል ታሪክ አላቸው። ከህልውና ስጋት ግን አልተረፉም። የኩርድን ጉዳይ ለጊዜው እንተወውና ኦሮሞዎቹ በኢትዮጵያ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ያደረጉትን እንመልከት፦
ኦሮሞዎች በ1522 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ ጊዜ ጀምሮ የከብት ጭራ እየተከተሉ በመጓዝ ነባር ሰላማዊ የኢትዮጵያ ብሔሮችን አጥፍተዋል። በገዳ ማህበር መመሪያ መሰረት ‘ገበሮ’ እና ‘ሞጋሳ’ በሚሉት መውረሪያ ስልታቸው የበርካቶችን ባህል፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት ብሎም ጥቅል ማንነት አጥፍተዋል። ዛሬ ኦሮምኛ የሚናገሩትና በዳሳ፣ ጃቢሳ ቅብጢሳ የሚባሉት ትውልዳቸው ወደ ኋላ ቢዘረዘር ኦሮሞዎች አይደሉም። በሞጋሳና ገበሮነት ማንነታቸውን የተነጠቁ ናቸው። ዛሬም በኦሮሚያ መስተዳድር ውስጥ የሚኖሩ ጉራጌዎች የቀበሌ መታወቂያቸው ላይ ብሔራቸውን ‘ጉራጌ’ ብለው ማስፃፍ አይችሉም። ጉራጌኛ እየተናገሩ ‘ኦሮሞ’ ተብሎ ነው የሚፃፈው።
በኦሮሞ ተወላጁ የነጋሶ ጊዳዳ ጥናት መሰረት በሰዮ ወለጋ አካባቢ ብቻ ሞጋሳ ከአሥር በላይ ነባር የኢትዮጵያ ነገዶችን አጥፍቷል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ካንቺ፣ ኮንቺ፣ ሙጩኮ፣ ጋንቃ፣ ወራጎ፣ ዳምታ፣ ካዛ፣ አጋዲ፣ ገበቶ፣ መጀንግ፣ ክወራ፣ ክዋማ እና ቡሳሴ ተጠቅሰዋል፡፡ በሌሎች ጥናቶች መሰረት ደግሞ 28 ነባር ብሔሮች በኦሮሞ ወረራ ጠፍተዋል።  ከ28ቱ መካከል ጋፋት፣ ማያ፣ አንፊሎና ወርጅህ ይገኙበታል፡፡ እነኝህ ነገዶች ከነቋንቋቸውና ሌሎች ማንነቶቻቸው ቁጥራቸው ቀስ በቀስ እንዲቀንስና ፈፅሞ እንዲጠፉ የተደረጉት የገዳ  ማህበር ባመጣው ወረራ እንደሆነ ዶክተር ሀብታሙ ተገኘ ‘በራራ ቀዳሚት አዲስ አበባ’ በተሰኘው መፅሀፋቸው አብራርተዋል፡፡ በተለይ የማያ ብሔር በዛሬው ናዝሬት፣ ደብረ ዘይትና ሽንብራ ኩሬ (ሞጆ) አካባቢ በስፋት ይኖር የነበረ እና በጦርነት ብቃቱ የተመሰከረለት ነበር።
የኦሮሞ ወረራ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ባደረገው ወረራ ክፉኛ የተዳከሙት የሺናሻ፣ የዘይ፣ የአርጎባ እና የማኦ ማሕበረሰቦችም በመጥፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ የሞት አፋፍ ላይ ናቸው ማለት ይቻላል፡፡
በዚህ ወቅት በተለይም ከአራት ዓመት በፊት ጀምሮ ኦሮሞ ያልሆኑትን ሁሉ በመግደል፣ ንብረታቸውን በመዝረፍና በማቃጠል እየተፈፀመ ያለው  እንቅስቃሴ ተቋርጦ የነበረውን የወረራ ዘመቻ ለማስቀጠል ያስቀጠለ ድርጊት ነው፡፡ ‹በአዲስ አበባ ተቋርጦ የነበረው የኢሬቻ በዓል ከ150 ዓመታት በኋላ ዳግም መከበር ጀመረ› እንደተባለው ሁሉ ‹ተቋርጦ የነበረው የገዳ የመስፋፋት ዘመቻ ተጀመረ’ ተብሎ ስላልተነገ እንጂ ወረራውና ጭፍጨፋው በተለይም በአማራ ላይ መፈፀም ከጀመረ ቆይቷል።
Filed in: Amharic