>

የአሮጌው አመት "የብልጽግና" በረከቶች....! ወግደረስ ጤናው

የአሮጌው አመት “የብልጽግና” በረከቶች….!

ወግደረስ ጤናው


~ ከ7ሺህ በላይ አማሮች በግፍ በኦነግ ኦሮምያ(ወለጋ) በሚባለው አካባቢ የታረዱበት እና ከ500 ሺህ በላይ ንፁሃን ከቤታቸው ተፈናቅለው ጎዳና የሚገኙበት፣

~ በኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ ከ20 ሚሊየን በላይ ንፁሃን ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው ዛሬ ላይ በመጠለያ ጣቢያዎች በዕርዳታ ስንዴ አዲስ ዓመትን የተቀበሉበት፣

~”ሁለተኛው እና ሦስተኛው ምዕራፍ” እየተባለ በሰሜን ኢትዮጵያ የእርስ በርስ ጦርነት ሺዎች ያለቁበት፣ሚሊየኖች የተፈናቀሉበት፣ሺዎች የቆሰሉበት፣በኢትዮጵያ ገንዘብ የማይተመን የሀገር ሃብት የወደመበት፣

~ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ፣አማራ ደግሞ አንደ ህዝብ የመጥፋት አደጋ በግልፅ የታየበት፣የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብ በጎሳ ተከፋፍሎ እርስ በርስ የተጨራረሰበት፣

~ በኢትዮጵያ በተለይም የአማራ ህዝብ ጭፍጨፉ ተለምዶ “ስንት ሞተ?” እየተባለ ቁጥር ብቻ የሆነበት፤ሰው የረከሰበት፣ሞት የረከሰበት፣ስደት እና መፈናቀል የበዛበት፣

~ አድር ባይነት፣ፍራቻ፣ነውር፣ስርቆት፣ማስመሰል ባህል የሆነበት፤

የሀገር ፍቅር ጠፍቶ፣የጎጥ ፍቅር ነግሶ የታየበት፣ሰዎች በእምነታቸው እና በመንፈስ ቀጭጨው በቁስ እና በስጋ ሰቀቀን የወደቁበት፣

~ አዲስ አበባ በኦህዴድ ተረኛው ስርዓት በኃይል ልትሰለቀጥ አፍ ውስጥ የገባችበት፣ህፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉበት፣

~ ከ20ሺ በላይ ጋዜጠኞች፣ጦማሮች፣ ማህበረሰብ አንቂዎች፣የዮኒቨርስቲ ሙሁራን እና ተማሪዎች፣ሀገር ጠባቂ ፋኖዎች፣የፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባለት በኦህዴድ ማጎሪያ ቤት ታግተው አዲስ አመትን ያሳለፉበት

~የሀገር ጠባቂ ፋኖዎች፣ለሀገር የሚቆረቆሩ፣የስርዓቱን ነውር እና ተረኝነት የሚያወግዙ ጀግኖች በሙሉ ከመኖሪያቸው የተሰደዱበት፣በየጫካው የተበተኑበት፣አባት ከልጆቹ፣ልጆች ደግሞ ከቤተቦቻቸው የተለያዩበት ዓመት፣

~ በኢትዮጵያ ህዝብን የሚመራ ሳይሆን በዘር ተቧድኖ አገር የሚዘርፍ እና የሚያፈርስ፣ድንቁርና የተጠናወተው ነውር ዐልባ ስርዓት የተጫነበት ጊዜ ነበረ።

2015 ነውረኞች ቦታቸውን አግኝተው በየጫካው ያሉ ሀቀኞች ሀገሪቱን የሚረከቡበት ዘመን ይሁን!!!

አሜን!!

Filed in: Amharic