የአሮጌው አመት “የብልጽግና” በረከቶች….! ወግደረስ ጤናው

የአሮጌው አመት “የብልጽግና” በረከቶች….!

ወግደረስ ጤናው


~ ከ7ሺህ በላይ አማሮች በግፍ በኦነግ ኦሮምያ(ወለጋ) በሚባለው አካባቢ የታረዱበት እና ከ500 ሺህ በላይ ንፁሃን ከቤታቸው ተፈናቅለው ጎዳና የሚገኙበት፣

~ በኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ ከ20 ሚሊየን በላይ ንፁሃን ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው ዛሬ ላይ በመጠለያ ጣቢያዎች በዕርዳታ ስንዴ አዲስ ዓመትን የተቀበሉበት፣

~”ሁለተኛው እና ሦስተኛው ምዕራፍ” እየተባለ በሰሜን ኢትዮጵያ የእርስ በርስ ጦርነት ሺዎች ያለቁበት፣ሚሊየኖች የተፈናቀሉበት፣ሺዎች የቆሰሉበት፣በኢትዮጵያ ገንዘብ የማይተመን የሀገር ሃብት የወደመበት፣

~ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ፣አማራ ደግሞ አንደ ህዝብ የመጥፋት አደጋ በግልፅ የታየበት፣የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብ በጎሳ ተከፋፍሎ እርስ በርስ የተጨራረሰበት፣

~ በኢትዮጵያ በተለይም የአማራ ህዝብ ጭፍጨፉ ተለምዶ “ስንት ሞተ?” እየተባለ ቁጥር ብቻ የሆነበት፤ሰው የረከሰበት፣ሞት የረከሰበት፣ስደት እና መፈናቀል የበዛበት፣

~ አድር ባይነት፣ፍራቻ፣ነውር፣ስርቆት፣ማስመሰል ባህል የሆነበት፤

የሀገር ፍቅር ጠፍቶ፣የጎጥ ፍቅር ነግሶ የታየበት፣ሰዎች በእምነታቸው እና በመንፈስ ቀጭጨው በቁስ እና በስጋ ሰቀቀን የወደቁበት፣

~ አዲስ አበባ በኦህዴድ ተረኛው ስርዓት በኃይል ልትሰለቀጥ አፍ ውስጥ የገባችበት፣ህፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉበት፣

~ ከ20ሺ በላይ ጋዜጠኞች፣ጦማሮች፣ ማህበረሰብ አንቂዎች፣የዮኒቨርስቲ ሙሁራን እና ተማሪዎች፣ሀገር ጠባቂ ፋኖዎች፣የፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባለት በኦህዴድ ማጎሪያ ቤት ታግተው አዲስ አመትን ያሳለፉበት

~የሀገር ጠባቂ ፋኖዎች፣ለሀገር የሚቆረቆሩ፣የስርዓቱን ነውር እና ተረኝነት የሚያወግዙ ጀግኖች በሙሉ ከመኖሪያቸው የተሰደዱበት፣በየጫካው የተበተኑበት፣አባት ከልጆቹ፣ልጆች ደግሞ ከቤተቦቻቸው የተለያዩበት ዓመት፣

~ በኢትዮጵያ ህዝብን የሚመራ ሳይሆን በዘር ተቧድኖ አገር የሚዘርፍ እና የሚያፈርስ፣ድንቁርና የተጠናወተው ነውር ዐልባ ስርዓት የተጫነበት ጊዜ ነበረ።

2015 ነውረኞች ቦታቸውን አግኝተው በየጫካው ያሉ ሀቀኞች ሀገሪቱን የሚረከቡበት ዘመን ይሁን!!!

አሜን!!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.