>

መነበብ ያለበት የመምህር ዘመድኩን በቀለ "ርዕሰ አንቀጽ"

“ርዕሰ አንቀጽ”

•ኦሮሙማው “…በትግራይ ትምህርት ቤት አውድመዋል። ተማሪም አስተማሪም ጨፍጭፈዋል። በሕወሓት ዥልጥ ኋላ ቀር ደባሪ፣ ቀፋፊ ያልሰለጠነ ገተት ቦለጢቃም መምህራን ሳይቀር በጦርነቱ ተሳትፈው በጅምላ አልቀዋል። ገሚሱ አካል ጉዳተኛ ሆኖ በቤቱና በካምፕ ተቀምጧል። ከጦርነቱ መቆየት፣ ከራብና ከጥሙ የተነሣ ደሞዝ የሚከፍላቸው በመጥፋቱም በሕይወት የተረፉትም የትግሬ መምህራን ነፍሳቸውን ለማቆየት ሲሉ ከክልላቸው ተሰደዋል። አሁን ትግራይ በትምህርት ልማት በኩል ብቻ ሳይሆን በሁሉም ረገድ ጨለማ ውስጥ ናት። ከዚህ የተነሣ ኦሮሙማው ትግራይን የመሃይሞች መናሃሪያ አድርጓት ህወሓትን የኦሮሙማው ገረድ ከመሆን ውጪ ሌላ አማራጭም ምርጫም እንዳይኖራት በማድረግ ዓላማውን በሚገባ አሳክቷል። የሆኑ የትግሬ አክቲቪስቶች ወይም ቦለጢቀኞች ኦሮሙማ ወንድማችን ነው ዐማራ ጠላታችን ሲሉ ብትሰሙ እንዳትፈርዱባቸው። አማራጭ የሌለው ግርድና ስለገቡ ነው።

“…ኦሮሙማዎቹ ነገ ሊፈጥሩ ላሰቡት ሀገረ መንግሥታቸው ግንባታ ለ3ሺ ዘመናት ኢትዮጵያን እየተፈራረቀ አስተዳደረ፣ መራ የሚሉትን ሰሜናዊ ነገድ ከትምህርትም፣ ከባንክና ከታንክም አካባቢ በማራቅ የኦሮሙማው ግዙፍ ፕሮጀክት ተግባራዊ በማድረግ ላይ ናቸው። ለዚህ ደግሞ ከእነሱ ነገድ ያልሆነ ነገር ግን ለሆዱ አዳሪ፣ በሥልጣን ጥም የተመታ ተባባሪ፣ ጉዳዩን አስፈጻሚ ገረድ በብርቱ ይፈልጉ ነበር። ሲፈልጉም ቆይተው ነው ብርሃኑ ነጋ ቦንገር የተባለ ከይሲ ፀረ ኢትዮጵያ፣ በግንቦት 7 ማኒፌስቶ ላይ ሥልጣን ከሰሜን ወደ ደቡብ መሸጋገር አለበት ብሎ ትግል የጀመረን ትውልድ ገዳይ ወደል ፀረ ሴማዊ ግለሰብ አግኝተው በማምጣት የትምህርት ሚንስቴር በማድረግ ህልማቸውን በመፈጸም ላይ ይገኛሉ። 12 ተማሪ አለፈ ብሎ ጋዜጠኛ ሲስቅ እንደ ጀነራል አድርጎት ምን ያስቅሃል በማለት ሄጵ ልበል የሚል ከንቱ። የኤርትራ ፍየል ጠባቂ ሳይተኩስ ጀግና፣ ተወዳድሮ ወድቆ ሚንስትር የሆነ ጥመኛ።

“…ሰውየው አሁን ኦሮሙማው የሚፈልገውን በሚገባ እያሳካለት ነው። የዐማራ ልጆች ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ፈተና መቀመጥ አይችሉም። ተፈትነው እንዲወድቁ ይደረጋሉ። ተፈትነው አልፈው ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲሄዱም ደግሞ ከመንገድ ላይ በኦሮሞ ነፃ አውጪዎች ይታፈናሉ፣ ይገደላሉ፣ ይደበደባሉ፣ ይወገራሉ፣ ይሰወራሉ። በመምህራኖቻቸው የሥነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው ይደረጋሉ። ከጾታዊ ጥቃት አልፎ ውጤታቸው በኤፍ ይተካል። በአካባቢው ማኅበረሰብ ወኪል ነን ባይ ቦለጢቀኞችም የተለያየ ጫና ይደርስባቸዋል። ስትሬት A ያመጡ ጂንየስ የዐማራ ተማሪዎችን በተለያዩ ዘዴዎች ይገድላሉ። ከፎቅ ወርውረው፣ በጩቤ፣ በሜንጫ ገድለው፣ ረብሻ አስነስተው በፖሊስ ዱላ ጭንቅላታቸውን በርቅሰው፣ ኩላሊታቸውን አፍርሰው፣ አይናቸውን አፍርጠው፣ እግርና እጃቸውን በቆመጥ ሰባብረው ሽባ፣ በሽተኛ አድርገው እንዳይሞት እንዳይድንም አድርገው ያስቀራሉ። ይሄ አንደኛው ዘዴአቸው ነው።

“…በዚህ የተነሣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዐማሮች ትምህርት አቋርጠው ወደ ክልላቸው ተመልሰዋል። ለቤተሰብም ሸክም ሆነዋል። አእምሮአቸው ተነክቶ ፀበል ለፀበል የሚንከራተቱና ለነጋዴ አጥማቂዎች ገረድ፣ ለፓስተር፣ ለሃኪምና ለጠንቋይ የገቢ ምንጭ የሆኑም የትየለሌ ናቸው። የተሰደዱም እልፍ ናቸው። ሥራ አጥ ሆነው በየማጎሪያ ካምፑ የገቡም ቀላል አይደሉም። ለመኖር ሲሉ አማራጭ ሲያጡ መከላከያም የገቡ እና እየተማገዱ ያሉም ብዙ ናቸው። የበራላቸው ደግሞ ለውጥ ለማምጣት ብረት አንስተው ይሄን አፓርታይድ መንግሥት ለመፋለም ጫካ የገቡም ጥቂት አይደሉም። የእነዚህ ምርጫ ግን የተቀደሰ ነው።

“…አሁን አፋር ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። አዲስ አበባን ኦሮሞ ለማድረግ በሚደረገው ፍትጊያ ከሚማሩበት ቀን የሚዘጋበት ቀን ይበልጣል። ዐማራ ጦርነት ላይ ነው። ወያኔም መጥታ አውድማው የሄደችው አፋርና ዐማራን ነው። አሁንም አቢይ አሕመድ የመከላከያ ሠራዊቱን በየትምህርት ተቋማቱ አስፍሮ፣ የተማሪዎች መቀመጫ ወንበርና ጥቁር ሰሌዳውን ሳይቀር ፈልጦ አንድዶ ኦና በማስቀረት በተጠና መልኩ ዐማራንም እንደ ትግሬ አፈር ከደቼ አብልተው ባዶውን እያስቀሩት ነው። እንደ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ሁመራና ዳንሻ አካባቢማ መምህራኑ ደሞዝ የላቸውም። ተማሪዎችም ወታደር ሆነዋል። ገሚሱም ተሰዷል። ጦርነትና ድርቅ የነቀላቸውም የትየለሌ ናቸው።

“…በወለጋም በምዕራቡ ክፍል ዐማራን አጽድቶ ትምህርት እየሰጠ ቢሆንም እንደ ሸዋ፣ አሩሲና ጅማ ኦሮሞ ውጤታማ አይደለም። አሁንማ ነፃ አውጪ ጦራቸው በዚያ ስላለ ትምህርት የለም። ምሥራቅ ወለጋ ዐማሮች ስለሚበዙ ዐማራን ከሁሉም ዘርፍ በማራቅ ፖሊሲው መሠረት ትምህርት ካቆሙ 5 ዓመት እየሞላቸው ነው። ህክምና፣ ቴሌኮሚዩኒኬሽን፣ መንገድ፣ ባንክ ወዘተ ካገኙም ቆዩ። መብራትም፣ ነዳጅም ስለሌለ ወፍጮ ቤቶች ባለመኖራቸው ሴቶቹ በድንጋይ ወፍጮ መፍጨት ከጀመሩ ቆዩ። እንዲህ አድርጎ እንደ ትግሬና እንደ ወለጋ ዐማራ ሁሉን ማውደምና ማደንቆር መሃይም ማድረጉ ላይ ከተሳካለት ኦሮሙማው በሌሎቹን ድንቁርና ላይ ዕውቀት ገንብቶ፣ በሃብትም ደርጅቶ እሱ ሳይንቲስት ሊቃውንት ኢንቨስተር ሊያፈራ ሌላው እከካም ደሀ ሆኖ እያከከ ሊያኖር መሆኑ ነው።

“…በሌሎቹ ክልሎች የጦርነት ድግሥ፣ አርቴፊሻል ሰው ሰራሽ ድርቅ እና ራብ፣ ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በመከልከል ፍጹም አረመኔያዊ በሆነ ጭካኔ የሰሜኑን ክፍል በተለይም ዐማራውንና ትግሬውን በመሃይሞች ሞልቶ፣ እርሱ ግን ክልሉን በተማረ የሰው ኃይል ሞልቶ አጥለቅልቆ ያልተማሩ ዐማሮችን እና ትግሬዎችን ለሚቀጥሉት 3ሺ ዘመናት ሌንጮ እንዳለው ሊገዙት አቅደዋል። ይሄ ገብቶት ለመቀልበስ የሚታገል ዐማራ እጅግ በጣም ጥቂት ነው። ገና ረኸጥ የሆነው የትየለሌ ነው። ሃዘን መከራ ከቤት ከመንደሩ ሲገባ ብቻ የሚባትት ነው የሚበዛው። ትግሬው በአምልኮ ህወሓት የተጠመቀ ስለሆነ የዐማራን መውደቅ፣ የወልቃይት እና ራያን መሬት እያሰበ ሲዝረከረክ በኦሮሙማው ተበልቶ አርፎታል። ቁማሩን ተበልቷል። ዐማራ ግን ተናንቆ ይዞታል። አይፋታውምም።

“…ሰሞኑን አንድ ነገር ታዘብኩ። ቀደም ሲል የትግሬና የዐማራ ልጆችን ለማቀራራብ ሃሳብ አፍልቄ የትግራይ ምሁራንና የትግራይ ጋዜጠኞችን በቴሌቭዥን መርሀ ግብሬ ለማቅረብ ሞክሬ ነበር። በወቅቱ ትግሬዎቹ በንዴት ላይ ስለነበሩ፣ ዐማሮቹም ከብልግና ጋር በጫጉላ ሽርሽር ላይ ስለነበሩ ሃሳቤ ውድቅ ነበር የተደረገው። ትግሬዎቹ እንግዶቼ የነበሩትን እነ ፕሮፌሰር ገላውዲዎስን አጥረግርገው ሰድበው ነው አሸማቅቀው ያባረሯቸው። እኔንም ከፍ ዝቅ አድርገው ነው ሃሳቤንም ውድቅ ያደረጉት። ትግሬና ዐማራ የጎንዮሽ ሽኩቻውን ትተው አንድ ላይ ካልቆሙ በአጭር ጊዜ ይበላሉ ነበር ያልኩት። እየሆነ ያለውም እንደዚያው ነው።

“…አሁን ግን አንዳንዳንድ ደፋር የትግራይ ልጆች ገዳያችን “የጋላው አገዛዝ ነው” በማለት ኦሮሞ የሚለውን ኦሮሞዎቹ ሊጠሩበት የሚፈልጉትን ስም ትተው በቀደመው የኦሮሞ ስም ጋላ በሚለው በመጥራት በድፍረት ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ወደ ሚድያ እየመጡ በአደባባይ ሲሞግቱ እያየሁ ነው። የጨፈጨፈን የኦሮሞ መንግሥት ነው። በምን ሂሳብ ነው እኛ ላይ ጭፍጨፋ የፈፀመው ዐማራ ብቻ ነው የምንለው። ኦሮሞዎቹ አይደሉም እንዴ በእኛ ላይ ያን ሁሉ ግፍ የፈጸሙት፣ ሰንጋ ገዝቶ የላከ፣ በሻሻ አድርገናቸዋል፣ ከፈለጉ ድንጋያቸውን ይዘው ይገንጠሉ ወዘተ ያሉን፣ በድሮን፣ በጀት፣ በምድር ጦር የወገሩን እነርሱ አይደሉም ወይ? ባጫ ደበሌ ገባ መቀሌ ብለው ዘፍነው…ቀድመው መቀሌስ የገቡትስ የኦሮሞ ሚዲያዎች አይደሉም ወይ…? ፋኖ፣ ፋኖ እያሉ በእኛና በዐማራ መሃል ቤንዚል ማርከፍከፉ ይብቃ በማለት ሲሞግቱ ታይተዋል። በዚህ ድርጊታቸው የተነሣም ኦሮሞዎቹ በትግሬዎቹ ላይ አዲስ የስድብ ዘመቻም ጀምረዋል። “ቁልቋላም፣ አንበጣ በሊታ” የሚለውን ስድብም ከደበቁበት ሰንዱቃቸው አውጥተው ትግሬዎቹ ላይ እያጎረፉባቸው ነው። የኦሮሞ አክቲቪስቶች የትግሬዎቹ ዐማራውን “ወንድሜ ነው” ማለትን አልደገፉትም። ደስም አላላቸውም።

“…ኦሮሞ በጎንደሬዋ የአቢይ ሚስት በኩል በኦሮሚያ “ኢፋ ቦሩ፣ ወይም የነገው ብርሃን” የተሰኘ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች በቢልዮን ዶላሮች ገንብተው የተማረ የሰው ኃይል እያፈሩ ነው። ኢፋ ቦሩ ከኦሮሞ ክልል አልፎ፣ በቤኒሻንጉል፣ በአፋር፣ በደቡብ፣ በጉራጌ፣ በጋምቤላ ሳይቀር በኦሮሚያ ክልል ወጪ እየተገነቡ ሥራ ከጀመሩ ቆዩ። ኦሮሞዎቹ እኛ የኮረጅነው ከትግሬዎቹ ነው። ትግሬዎቹ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ዘጭ አድርገው ከስክሰው ስብርብሩን አውጥተው ሲያበቁ እነርሱ ግን በትግራይ “ቀለሚኖ” የሚባል ትምህርት ቤት ከፍተው ተማሪዎችን በተለየ እንክብካቤ በማስተማር በመላዋ ሃገሪቱ እና በዓለምአቀፍ ድርጅቶች ሁሉ ተቀጣሪ፣ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን ተግባር ሲፈጽሙ ነው የኖሩት። ለትግሬ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ በማፈላለግ በአውሮጳና በአሜሪካ ጭምር እንዲማሩ በማድረግ ተጠቅመዋል። እኛም እንደዚያው ብናደርግ ምን አለበት ነው የሚሉት ኦሮሞዎቹ። ዐማራ ግን ልጁን ያላስተማረ ወዮለት እያለ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንዲማሩ ሲያደርግ መኖሩን እንደ ዥልጥ፣ ዥል፣ ፋራና ሰገጤ እንዲታይ ነው ያደረጉት።

“…ኦሮሙማው በዚህም አለ በዚያ ዐማራ እና ትግሬ በዋናነት፣ አፋር ሱማሌ ቀጥሎ፣ ደቡብም እየተከተለ እንዲሾቁ ተደርገዋል። ዘንድሮ ብቻ 1300 ትምህርት ቤቶች ከትምህርት ቤታቸው ከአጠቃላይ ተማሪዎች አንደኛ የሚወጡት ተማሪዎች ሳይቀር እንዳያልፉ ተደርገዋል። መምህራኖቹ አብደዋል። ቤተሰብ ተስፋ ቆርጧል። መከላከያ ደግሞ ወታደር በስፋት ለመቅጠር አሰፍስፎ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። አንደኛ እንኳን የሚወጡትን ተማሪዎች እንዳያሳልፉ በማድረግ ከቢዝነሱ እንዲወጡ እያደረጉ ነው። በአጠቃላይ ኦሮሙማው ክልሎችን በሻሻ በሚያደረግበት ሂደት ሁሉም ክልል ማትሪክን አይፈተኑም። ትምህርቤቶችም ይጋያሉ። ተረጋግተው ተማሪ ማስፈተን አይችሉም። በደብረታቦር፣ በደብረ ማርቆስ፣ በጎንደር የተፈጠረውን አስታውሱ።

“…ይሄ ሁሉ ፖለቲካዊ ጫና እያለባቸውም ቢሆን ግን የሚደንቀው ደግሞ አሁንም በዘንድሮው በ2015 ዓም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙ ካሳለፉ 5 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 3ቱ በዐማራ ክልል የሚገኙ መሆናቸው ነው የተነገረው። ደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት፣ ሀዲስ ዓለማየሁ ልዩ የአደሪ ትምህርት ቤት እና ባሕር ዳር ስቴም ትምህርት ቤት በስም ተጠቅሰዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ ሳይንስ ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው ተማሪም የሐዲስ ዓለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ መሆኑም ታውቋል። የዐማራ ክልል ትምህርት ቢሮ እንዳለው ከሆነ በሐዲስ ዓለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት እና በደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት በድምሩ 32 ተማሪዎች 600 እና ከዚያ በላይ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡ የናዝሬት አዳማው ግን አንድ ተማሪ ብቻ ነው የጣለው።

“…ልብ በሉ በዐማራ ክልል የሚማሩ ተማሪዎች የሚያሳልፉትን ፈተና። በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ክልሎች ባለፉት ዓመታት ያለ ዕዳው በሰላም እጦት ክፉኛ የተጎዳ ክልል ነው። ተማሪዎች የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተምረው የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተፈትነዋል፡፡ አብዘኛዎቹ የክልሉ ተማሪዎች በጦርነት ምክንያት በወደሙ እና በተዘረፉ ትምህርት ቤቶች ለመማር ተገድደዋል፡፡ በፈተና ወቅት አለመረጋጋት እንዳይፈጠር በማድረግ ተማሪዎች ፈተናውን አቋርጠው እንዲወጡ ተደርገዋል። እንዲህም ሆኖ ግን ሰንሰለቱን ሰብረው መውጣት እንደሚችሉ አሳይተዋል። ግን ውጤቱ በአዳሪ ትምህርት ቤቶች ላይ ብቻ ተገኘ ማስባሉ አልገብቶኝም። • ኦሮሙማው ቀጥሎ ምንድነው የሚያደርገው…?

1፦ ሌሎቹ ክልሎች ሲሾቁ የተማረው የኦሮሞ ቁጥር በሃገሪቱ ይበዛል። የተማረው የኦሮሞ ልጅ ሲበዛ ደግሞ ያልተማሩትን መሃይሞችን እንደ ባርያ በገዳ ሥርዓት ረግጦ ይገዛል።

2፦ ነባር እና ምርጥ ምርጥ ተማሪዎችን በማፍራት የሚታወቁት ስመጥር ትምህርት ቤቶችም እነ ዝናሽ ታያቸው እና ሽመልስ አብዲሳ በሚገነቡአቸው ትምህርት ቤቶች ይዋጣሉ። ይዋጡናም መምህራኖች በሙሉ ኦሮሞ ይሆናሉ። አዲሶቹ ትምህርት ቤቶችም ሌላ ስለማይቀጠሩ የትም ክልል ይሁን ባለቤት ስለሚሆኑና እና ሁሌም ከነባሮቹ ትምህርት ቤቶች ተማሪ ስለማያልፍ ተማሪው ምርጫውን እነ ዝናሽ እና ሽሜ ወደአሠሯቸው ትምህርት ቤቶች ይፈልሳሉ። እዚያ ሲሄዱ ደግሞ የሌለ ተጽዕኖ ይጠብቃቸዋል። የገዳን ሥርዓት፣ ቁቤ፣ አረብኛ፣ በግድ ይማራሉ። በዚያ አማርኛ መማርም፣ መናገርም ነውር ነው። ኦሮሚኛ A ያላመጣ ተማሪ ማትሪክ  ስለማያልፍ የሌላው ቤሔር ተማሪ በሙሉ ዕጣ ፈንታው ማሃይም መሆን ብቻ ነው። ዋጠው።

3፦ ትልቁና ወነኛው ትግል ግን አማርኛን ከኢትዮጵያ ማጥፋት ነው። ይሄ የኦሮሙማው ትግል ብቻ አይደለም። የምዕራባውያኑም ጭምር እንጂ። የዐማርኛ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ማስተሳሰር ምዕራባውያኑ አልተመቻቸውም። ስለዚህ አማርኛን ለማጥፋት እነ ሽመልስ አብዲሳ በቃል የነገሩንን በተግባር እያዋሉት ነው። ትግሬም ሳይገባው በጥላቻ እና በበታቸኝነት ስሜት ተጠምዶ ከትግራይ ክልል የአማርኛን ትምህርት መሰዙን አሳውቋል። ዥል። ኦሮሞ በላቲን ነው። ሲዳማ በላቲን ነው፣ ሱማሌ በላቲን ነው። አፋር በላቲን ነው ማስተማር የጀመሩት። ሁሉም ባሌን ጎዳሁ ብለው ይሉት ተረት እየፈጸሙ ነው። ክልሎች ሁሉ የአማርኛ ትምህርት ስለማይሰጡ የነሱ የትምህርት ቤቶች ቁጥሩ በእነ ሽመልስ አብዲሳ ትምህርት ቤቶች ስለሚዋጥ እንደ ዕቅዳቸው አማርኛን ያጠፉታል ማለት ነው። አዲስ አበባም ኦሮሚኛ መማር ግዴታ ሆኗል። ስለ ገዳ ሥርዓትና ስለ ኢሬቻ ሳይቀር ከመዋዕለ ሕጻናት ጀምሮ በግድ መስጠት ተጀምሯል። ወሎ ደቡቡ ክፍል ወደ ቁቤ በግድ እያስገቡት ነው። ይሳካላቸው አይሳካላቸው ባላውቅም እየሄዱበት ያለው አደገኛ መንገድ ግን ይሄው ነው።

“…የፋኖን ትግል ካልደገፍክ አዳሜና ሄዋኔ የግድህን ትወርማታለህ። እየቀለድኩ አይደለም። ትወርማታለህ አልኩህ ትወርማታለህ። በትግራይ ኢትዮጵያ የሚለው ስም ተፍቆ የቀረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚለው ብቻ ነው። ሰንደቅ ዓላማዋም ወርዷል። ተፍቋል። ተደምስሷል። ቤተ ክርስቲያን ላይ የቀረው ስምም በጋለሞቶቹ የትግራይ የህወሓት ኤክስ ጳጳሳት ተፍቆ የትግራይ ኦርቶዶክስ በሚል ተተክቷል። ከኦሮሚያም እንደዚያው። የቀረው ባንኪ ደልደላ ኢትዮጵያ ብቻ ነው። እናም አባቴ ኢትዮጵያንም ማንነትህንም የማዳኛው ጊዜ አሁን ነው። አንተ ቀልድ። ፈርሽ፣ ተዝናና። በኋላ ስትነቃ ትታነቃታለህ። • ይሄ የእኔ የዘመዴ እይታ ነው። የእናንተን ለመስማትም ዝግጁ ነኝ። ቆይቼ አንብባችሁ ስትጨርሱ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። እስከዚያው መልካም ቃሪያ በሚጥሚጣ የሆነ ንባብ።

ድል ለዐማራ ፋኖ…!

• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው…!

Filed in: Amharic