>

የኃላው ከሌለ የፊቱ የለም!!! ታሪክ አልባዋ ከተማ

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! የብ/ጀነራል የደም መሬት!

Bombard the Orommuma Headquarter!››

 (ክፍል ሦስት)

  ፂዮን ዘማርያም (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

የኃላው ከሌለ የፊቱ የለም!!! ታሪክ አልባዋ ከተማ

A City Without Its Past

‹‹ዘመቻ ውባንተ ወደ አዲስ አበባ እየገሠገሠ ነው!!!›› የአማራ ፋኖ በሸዋ ዕዝ አዛዥ ኮማንደር አሰግድ መኮንን

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! Bombard the Orommuma Headquarter!!!››

‹‹በሚፈርስ ከተማ ……….ነጋሪት ቢጎሰም………….አይሰማ!!!››

‹‹ወይ አዲስ አበባ፣ ወይ አራዳ ሆይ

አገርም እንደሰው ይናፍቃል ወይ!!!››

የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ለዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ለሽያጭ ቀርቦል!!! ዶላር ፍለጋ በጨረቃ!!!

ኮነሬል አብይ ለዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ኤግል ሒልስ ኩባንያ (Eagle Hills) 360000 (ሦስት መቶ ስልሳ ሽህ) ካሬ መሬት በነፃ በማበርከት ኤግልስ ሂልስ በሁለት ቢሊዮን ዶላር ፕሮክት ወጪ ህንፃዎች ለመገንባት ያለአንዳች ጨረታ ተሸልሞ  ምንም ሳይሰራ ስድስት አመታት አልፎታል፡፡   Eagle Hills is a private real estate investment and development company based in Abu Dhabi, United Arab Emirates. The company is headed by Mohamed Alabbar, founder and managing director of Emaar ለኤግልስ ሒልስ ፕሮጀክት ሲባል የፈረሱ ህንፃዎች የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ብዙ መቶ ሚሊዩን ብር የወጣበት አዲስ ህንጻ ፈርል፣ የቡፌ ደ ላጋር ታሪካዊ ባህላዊና ዘመናዊ የመዝናኛ ሥፍራ ፈርል፣ የቬርኔሮ ህንፃ ባለ ስድስት ፎቅ ህንፃ  ፈርል፡፡ ኦህዴድ ብልጽግና መንግሥት አብይ፣ አዳነች አቤቤ፣ ሥልጣን ከያዙ ጀምሮ የአዲስ አበባን ከተማ ንዋሪዎች በማፈናቀልና ቤታቸውን በማፍረስ  ከተማዋን ለመሸጥ ላይ ይገኛሉ፡፡ የህብረተሰቡን ሶሻል ፋብሪክ እድር ፣እቁብ፣ ፅዋ፣ ማህበር የመሳሰሉት ክፍለዘመናት ያስቆጠሩ ማህበራዊ ድርና ማግ ግንኙነቶች በማጥፋት ላይ ናቸው፡፡ Century-old social welfare institutions called Idir to break apart.

የአዲስ አበባ ከተማና ቅርስ አፍርሶ ሻ ለሰው ጁቦች!!! 

ኢንጅነር ዮናስ ታደሰ፡- ኦቪአይዲ ኮንስትራክሽን ድርጅት (OVID CONSTRUCTION PLC) በ2013 የተቆቆመ ሲሆን ዋና ማናጀሩም አቶ ዮናስ ታደሰ ሲሆኑ ካንፓኒው  የኮንስትራክሽን፣ ሪል ስቴት፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ትሬድ ሃውስ፣ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ ጤና፣ቬንቸር ካፒታልን አካቶ የሚሠራ ድርጅት ነው፡፡  በገርጂ ፕሮጀክቱ ለፌዴራል ሃውስንግ ኮርፖሬሽን ትዕዛዝ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የሚሠራው አስር አፓርትመንቶች ህንፃዎች ለ440 ቤቶች ያካትታል እየሠራ ይገኛል፡፡ GERJI FHC PROJECT Design and Build of 6 sky villas with 60 Units and 10 Apartment buildings with 440units proposed to Federal Housing Corporation to accommodate Ethiopian higher officials. It is designed in a manner that well-considered matters of design, security, functionality, and quality. በፍኖተሠላምና ሆሳዕና በኢትዮጵያ ፌዴራል ዴሞክራቲክ ሪፓብሊክ ትዕዛዝ ለብሔራዊ አደጋ መከላከያ ኮሚሽን የእህል መጋዘን (big-scale grain stores) በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ መርከብና ሎጂስቲክስ ኢንተርፕራይዝ በሞጆ ከተማ የአፈርና የማዳበሪያ መጋዘን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ኦቪአይዲ ኮንስትራክሽን ድርጅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ፕሮጀክት (ETHIOPIAN NATIONAL THEATER PROJECTስራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ 

ኮነሬል አብይ በአሬ ፕሮጀክታቸው  በገለፁበት ጊዜ በጥይት ቤት ጂ20 መንደር 1860 (አንድ ሽህ ስንት መቶ ስልሳ) የቤት ግንባታ ለኦቪአይዲ ኮንስትራክሽን ድርጅት (OVID CONSTRUCTION PLC) ዋና ማናጀር አቶ ዮናስ ታደሰ  ሠርቶ ሲያልቅ 600 (ስድስት መቶ ቤት) ለመንግሥት ያስረክባል ቀሪውን 1260 (አንድ ሽህ ሁለት መቶ ስልሳ) ቤቶች አቶ ዮናስ ታደሰ ሸጦ ይጠቀማል ብሎል፡፡ ኮነሬል አብይ እንዲህ ዓይነት ፈላጭ ቆራጭ አንባገነን መሪ ለመሆን በቅቶል፡፡ በኢትዮጵያ ምድር፣ የመንግሥት መሬትን በገዛ ፍቃዱ ይሠጣል፣ ያለ ምንም ጨረታና ውድድር ለጎደኞቹና ለአደግዳጊዎቹ መሬትና ሥራ ያበረክትላቸዋል፡፡ የኮነሬል አብይ የኦህዴድ ብልጽግና መንግስት የአዲስ አበባን ከተማ አፈራርሶ በመሸጥ ላይ ይገኛል ሥርዓቱ ግልፅ አሠራር የሌለው፣  በፓርቲ ወዳጅነት፣ በዘር ዝምድና ጥቅሻ የሚሠራ ሹማምንት ሃገራችንን የትም አያደርሱ፡፡

ኢንጅነር ጎሳዬ በቀለ ኮንፓስ ኮንሰልታንሲ ካንፓኒ፡- ለአዲስ አበባ አዲስ ዲዛይን እንደወጣና የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት አጥኝ ቡድን እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ የኮንፓስ ኮንሰልታንሲ ካንፓኒ ጥናት መሠረት አዲስ አበባ የኮሪደር ልማት መሠረት መንገዶችን ለማስፋት በሚል ብዙ ህንጻዎች እየፈረሱ እንደሆነ ይታወቃል እንዲሁም ጥንታዊ ታሪካዊ ቅርሶች እየፈረሱ እንደሆነ ሲታወቅ የኮንፓስ ኮንሰልታንሲ ካንፓኒ  በጥናት የተደገፈ ነው በማለት ሽንጣቸውን ገትረው በመከራከር ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መዋቅራዊ ጥናት በጨረታ ወጥቶ ስንት ካንፓኒዎች እንደተወዳደሩና ኮንፓስ ኮንሰልታንሲ እንዳሸነፈ ኢንጅነር ጎሳዬ በቀለ ቢገልፅልን ከሙስና የፀዱ ለመሆንዎ ምስከር ይሆንዎታል፡፡ ካንፓኒ ኮንሰልታንሲ ካምፓኒ ፕሮፋይል በድረገጽ የሌለው አዲስ ድርጅት ሲሆን፣ ኢንጅነር ጎሳዬ በቀለ ስለ ጥንታዊ ታሪካዊ ቅርስ በተመለከተ  ኢንጅነሩ ያላቸው የተዛባ አመለካከት ከባለሙያተኞች ጋር ቢወያዩ ሊያስረዱዎች ይችላሉ እንላለን፡፡ አዲስ አበባ ከተማን አሮጌዋና አዲሶ ብሎ በመክፈል አሮጌውን ሳያፈርሱ፣ አዲሶን አዲስ አበባ መገንባት ይቻል ነበረ፣ የወደመውን ንብረት ኮንፓስ ኮንሰልታንሲ ያጠናው ነገር ቢገልፁልን በተገባ ነበር፡፡  ኢንጅነሩ ቅይጥ የመሬት አጠቃቀም አንድን ህንፃ ለመኖሪያም፣ ለንግድና ለሌሎች አገልግሎት ማድረግ እንደሚቻል የገለፁት የእሳቸው ግኘት አድርገው መግለፅቸው ስራው በእውቀት ሳይሆን በችሮታ እንደተበረከተላቸው ያሳብቃል፡፡ አንድ ቀን ግን ተጠያቂነት በዚች ምድር ላይ አለ እንላለን፡፡  

‹‹ከላይ ሰውዬው፣ ከታች ገብርዬው፣ መኃል ንሳ ዝምብየው!!!››

ኮነሬል አብይ አህመድ የተለያዩ የግንባታ ሥራዎችን ፓርኮች፣ የጫካው ፕሮጀክት፣ አድዋ ዚሮዚሮ፣ የአሬ ፕሮጀክት፣ የወንጪ ዳንዲ፣ ሃላላ ኬላ፣ ጎርጎራ፣ኮይሻ፣ ጮርጮራ ወዘተ ፕሮጀክቶችን  ያለ አንዳች ጫረታ የሚያሠራው ለኦህዴድ ብልጽግና እሚያውቃቸው ጎደኞቹ መሆኑና ግልፅነት የሌለው፣ የዘር ጎደኝነት ላይ የተመሠረተ ስራ ሲሆን በአጠቃላይ መልካም አስተዳደር የሌለው ና አድሎና ሙስና የኦህዴድ ብልፅግና መንግስታዊ መዋቅር ውስጥ የተንሠራፋ የሥርዓቱ መገለጫ ሆኖል፡፡ ይህን በመሳረጃ ለማሳየት በቴሌቨዝን በሬዲዩ፣ በጋዜጦች ላይ የፕሮጀክቶቹ ሥራ አንድ ቀንም ጨረታ ወጥቶ እንደማያውቅ ይታወቃል፡፡ 

ፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ፡- በሀገሪቱ  እቅድ ወይም በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እቅድ ላይ ያልታቀደ ነው፡፡  የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት መሠረታዊ ዝግጅት የሌለው ህብረተሰቡን ያላሳተፈ፣ በጥናት ያልተደገፈ፣ የህብረተሰቡን ሶሻል ፋብሪክ ማህበራዊ ድርና ማግ እድር፣ እቁብ፣ ፅዋ፣ ማህበራትን ግንኙነት ህልውና ያናጋ፣ ኢኮኖሚያዊ አዋጭነት ያልዳሰሰ ፖለቲካዊ ውሳኔ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የልማት እቅድ አዋጭነት ጥናት ያልተደረገበት መሆኑን በማዘን ገልፀዋል፡፡   

ሌሎች የምጣኔ ኃብት ጠበብት ጥናት መሠረት የአዲሰ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት 1.5 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሽህ) ነዋሪዎችን ህይወት የሚያናጋ ነው፡፡  200 ሽህ ነባር ይዞታዎች  ይፈርሳሉ፡፡ ህብረተሰቡ ነባር ይዞታዎች እየፈረሱ ይገኛሉ፡፡ ህብረተሰቡ በልማቱ ጉዳይ በተመለከተ  ምንም ውይይት አልተደረገም፡፡  የኪነህንፃ  ጠበብት የአዲስ አበባ ጥንታዊና ታሪካዊ ቦታዎችን አለመጠበቃቸው  ባለሙያዎችን ያላሳተፈ ፈረሳ ነው፡፡ 

‹‹የተመዘገቡ ታሪካዊ ቅርሶች ኃብት በማይጠገን ፈረሳ ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አበባ ባህል፣ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ እንዳሉት ቢሮው ታሪካዊ ቅርሶች ኃብት እንደሚመዘግቡ ሆኖም ቀርሶቹን የማስጠበቅ ሥልጣን ወይም እንዳይፈርሱ ምንም ማድረግ ችሎታ የለንም፡፡›› “We usually hear issues regarding the demolition of historic treasures once irreparable damages have been made.” says a senior expert at Addis Ababa Culture, Arts & Tourism Bureau. Even though we register heritages, we neither have the mechanism to protect them nor the power to stop their demolition.

የጥንት ኪነህንጻ ጥበብ እንዳለ ማቆየት ጥንታዊ ህንፃዎች ሥነህንፃ አሰራር መጠበቅ ሲሆን ዘለቄታዊ የከተማ ልማት ቀጣይነት ያሳያል፡፡  This approach not only preserves the buildings’ architectural integrity but also contributes to sustainable development and revitalization of urban areas.

በከተማ ልማት እቅድ ፖሊሲ መሠረት ጥንታዊ ታሪካዊ ህንፃዎችን የህዝብ ውርስና ቅርስ ሆነው እንዲቀጥሉ በማድረግ ከዘመናዊ ኪ-ህንጻዎች ጎን ለጎን አዋህዶ ማስቀመጥ የህዝባችን ክብርና ሞገስ እንዲሁም የባለቤትነት ጥያቄ ነው፡፡ It is crucial to raise awareness about the value of historic buildings and promote a sense of pride and ownership among the public………The dramatic changes in the past three decades and the demise of much historic architecture are not anomalies. A vast urban makeover is continuing with the potential of making Addis Ababa a city without its past. About eight percent of the heritage buildings listed by the Culture, Arts, and Tourism Bureau have already been demolished. At the same time, there needs to be a mechanism and institutional arrangement to stop the damage further.

ታሪካዊ ቅርሶችን እያፈረሱ ዘመናዊ ህንፃዎችን መገንባት አላዋቂነት ነው፡፡ ለዚህ ነው የኃላው ከሌለ የፊቱ የለም!!! የሚባለው፡፡ አዲስ አበባን ታሪክ አልባ ከተማ A City Without Its Past ማድረግ የኦህዴድ ብልፅግና የፖለቲካ ሴራ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ውርስና ቅርስ ማጥፋትና የኦሮሙማን መትከል የኮነሬል አብይ፣ ሽመልስ አብዲሳና የአዳነች አቤቤ የጥላቻ ፖለቲካ ውጤት ነው፡፡ ይህ የከተማ ቅርስ ማውድም፣ በታሪካዊ ቅርሶች ኃብት ላይ አጠቃላይ ውድመት አስከትሎል፡፡ ጥንታዊ ህንፃዎች የከተማዋን ታሪክ፣ ባህልና፣ ማንነት ያሳያል፣ይገልፃል፡፡ ቅርሶቹ ተጨባጭ ኃብት በመሆን ለአገር ጎብኝዎች የሃገሪቱን ጥንታዊ ኪነ-ህንጻ አሰራር ቅርፅና ውበት የሚያሳዩ የጥንት ማንነታችን መገለጫዎች ናቸው፡፡ የከተማ እድገትና ዘመናዊነት ለኢኮኖሚ እድገትና ስልጣኔ የሚያበረክቱት አስተዋፅኦ እንዳለ ሁሉ ጥንታዊውንና ዘመናዊውን ሚዛናዊ በማድረግ ታሪካዊ ቅርሶችን መንከባከብን ከዘመናዊ ህንፃዎች ጋር አዋህዶ መስራት የኃላውን ከፊቱ ጋር ማዛመድ ያስፈልጋል እንላለን፡፡ Demolition of old urban spaces and redevelopment into a completely new urban look has become a common trend in Addis Ababa. This practice brings enormous collateral damage to the city’s heritage. Historic buildings play a vital role in showcasing a city’s history, culture, and identity. They serve as tangible reminders of the past and contribute to a city’s overall aesthetics and character. While urban development and modernization are essential for economic growth and progress, it is equally important to strike a balance between preserving historic buildings and constructing modern infrastructure.

አርክቴክት ፋሲል ጊዩርጊስ፡- የከተማ አርክቴክቸራል ሄሪቴጅ ጥበቃ ኃላፊ በኢትዮጵያ ኢንስቲቲዩሸን ኦፍ አርክቴክቸራል ቢውልዲንግ ኮንስትራክሽን እንዲሁም የከተማ ልማት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኃላፊ ሲሆን ትልቁ ተግዳሮት የጥንታዊ ቅርስ ሃብታችንና እሴት   ምን ያህል ዋጋ እንዳለው  ንቃተ,ህሊና አለመኖር ነው፡፡‹‹ ይሄ አሮጌ ቤት ሰፊ ቦታ ይዞል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ቅርሱን ቤቱን አፍርሶ መሬቱን ሸንሽኖ የመሸጥ ፍላጎት አለው፡፡›› ፋሲል እንደሚተነትነው ዋናው ጉዳይ የቤቱ ቀርስነት ምንም ዋጋ አያወጣም፣ የእውቀት ድህነትና ማነስ፣ ቅርሱ ሳይፈርስ እንዴት መጠቀም እንችላለን? According to Fasil Giorghis, the Chair of Conservation of Urban & Architectural Heritage at the Ethiopian Institute of Architecture Building Construction & City Development at Addis Ababa University, a significant challenge we face is the need for awareness regarding the value of our heritage. He explains, “These old houses occupy large areas, and the administration often chooses to demolish them simply because they desire the land they sit on.” Fasil emphasizes that the real issue lies in the assumption that these buildings have no worth and lack knowledge on how to utilize them without demolition……………………..(1) (1)

ዶክተር ሱራፌል ወንድሙ ፡-‹‹ዛሬ በአደባባይ ስለማኅበራዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እውነት እንድንነጋገርና ውሳኔያችንን በጋራ ያማረ እንድናደርግ ለሁላችንም በተለይ ለመንግሥት የሚደረግ ጥሪ ነው። ይህንንም ተንተርሼ ስለሐኪም ወርቅነህ እሸቴ ቤት ታሪካዊነት እመሰክራለሁ። ምክንያቱም ቤታቸው በቅርስነት ተመዝግቦ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ቅርስነት የላቸውም ተብለው መፍረስ ከተፈረደባቸው መሀከል ሆኗል። 42 በቅርስነት የተመዘገቡ ሕንፃዎች ውስጥ 36 ይፈርሳሉ የሚለው መርዶ ያስደነግጣል። ጥያቄው ደርሶ የመንገድና የሕንፃ፣ የቅርስና የቴክኖሎጂ ግንባታ ብቻ እንዳልሆነ፤ ይልቁንም በዚህ ዘመን ሰው መሆን ምንድነው ብለን እንድንጠይቅ ያሳስበናል። ሁኔታውን ሊረዱ የሚሹ ቀና ልቦች ካሉ በአክብሮት ተነጋግሮ ውሳኔን ለማስከለስ። ሁኔታውን ከቅርስም ባሻገር የነፃነት ጥያቄ አድርጎ በማየት፣ የአጠቃላይ የከተማ ልማትን ጉዳይ ከሥሩ እንዲጠራ ማድረግ መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን በማስመር ርዕሴን ተከትዬ ስለሐኪም ወርቅነህ እጽፋለሁ። ይህ ምስክርነት የግለሰቡን የዶ/ ወርቅነህ እሸቴን ስም የማንቆለጳጰስ፣ የታላላቅ ሰዎችን የከፍተኛ መደብ ሕይወት የማስተጋባት፣ ወደ ትላንት ብቻ ከሚያነጉድ ትዝታ ጋር በፍቅር የመነሁለል ድሮ ናፋቂነት አይደለም። ታሪክን የምመለከትበት ዕይታ ከቶውኑም እዚያ እንድገኝ አይፈቅድልኝም። ይልቁንም በስተመጨረሻ የሐኪም ወርቅነህ እሸቴ ሕይወት የተቋጨባቸው መኖሪያ ቤቶቻቸው የኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፣ የዓባይ ግድብና የባህር በር ታሪክ፣ የፀረ ባርነትና የፀረ ቅኝ ግዛት ትግልና የትምህርት ማስፋፋት ታሪኮችን አትመው ማቆየት የሚያስችሉ ሙዚየሞች ናቸው (ሊሆኑ ይገባቸዋል) ከሚል መነሻ ነው።›› ከድረገፁ መነበብ የሚገባው ጹሁፍ ነው……………………………………………….(2) 

የደም መሬት፡- አዲስ አበባን አፍርሰው ለጀነራል መኮንኖች ለመስጠት መሆኑ በተግባር ታይቶል፡፡ 

{1} /ጀነራል   ሙሉ ሞገስ መኮንን፣ንፋስ ስልክ 800 ካሜ

{2} /ጀነራል   አዱኛ ዴሬሳ ሆሬሳ፣ ኮልፌ 800 ካሜ

{3} /ጀነራል   ማርዬ በየነ አስናቀ፣ ቦሌ 800 ካሜ

{4} /ጀነራል   ገዛህኝ ፍቃዱ በቀለ፣ ንፋስስልክ 800 ካሜ

{5} /ጀነራል   ተመቸው ተስፋዬ አበራ፣ ንፋስስልክ 800 ካሜ

{6} /ጀነራል   ደረጀ ደመቀ ማሞ፣ ቦሌ 800 ካሜ

{7} /ጀነራል   ጀመል ሻሌ ዱሌ፣ ኮልፌ 800 ካሜ

{8} /ጀነራል   አበበ ዋቅሹም ተሬሳ፣ ንፋስስልክ 800 ካሜ

{9} /ጀነራል   ደርቤ መኩሪያ አዲሱ ኮልፌ  800 ካሜ

{10} /ጀነራል   ተሸመ አናጋው አያና ኮልፌ  800 ካሜ

{11} /ጀነራል   ከማል አቢሶ አንተሌ ንፋስስልክ  800 ካሜ

{12} /ጀነራል   አማረ ባህታ በርሄ፣ ኮልፌ  800 ካሜ

{13} /ጀነራል   ሀብታሙ ምህረቴ በየነ፣ ቦሌ  800 ካሜ

{14} /ጀነራል   ተስፋዬ ለገሠ ዲያና ኮልፌ   800 ካሜ

{15} /ጀነራል  ዋለልኝ ታደስአዛለ፣ ቦሌ  800 ካሜ

{16} /ጀነራል   ሰይፈ ኢንጊ ጉራሮ፣ ቦሌ  800 ካሜ

{17} /ጀነራል   መሃመድ ሁሴን እንድሪስ፣ ንፋስስልክ 800 ካሜ

{18} /ጀነራል    ኃሸም መሃመድ ጭቆላ፣ ኮልፌ  800 ካሜ

{19} /ጀነራል   ንጉሴ ሚዔሶ ጁባ፣ቦሌ 800 ካሜ

{20} /ጀነራል   እሸቴ አራጌ ሞገስ፣ ኮልፌ  800 ካሜ

{21} /ጀነራል   አዲሱ መሃመድ ጸዳል፣ ንፋስ ስልክ 800 ካሜ

{22} /ጀነራል   ታዬ አለማየሁ ገዛህኝ፣ ኮልፌ 800 ካሜ

{23} /ጀነራል   አምሳሉ ኩምሳ ሮሮ፣ ቂርቆስ  800 ካሜ

{24} /ጀነራል   በስፋት ፈንቴ ተገኝ፣ ቂርቆስ  800 ካሜ

{25} /ጀነራል   አበበው መንግስቴ ሰርጨው፣ ቦሌ  800 ካሜ

{26} /ጀነራል   ሶፊያን ሸክ መሃመድ ከሊፋ፣ ኮልፌ   800 ካሜ

{27} /ጀነራል   አርቃሌ ዱካቶ ጋጌ፣ ንፋስ ስልክ 800 ካሜ

{28} /ጀነራል   ተክሉ ሁርሳ ጅንካ፣ ቂርቆስ  800 ካሜ

{29} /ጀነራል   አዱኛ ዴሬሳ ሆሬሳ፣ቂርቆስ  800 ካሜ

{30} /ጀነራል   ተመስገን ማሎሬ ግዶሬ፣ ንፋስ ስልክ 800 ካሜ

{31} /ጀነራል   ከማል አቢሶ አንተሌ፣ ንፋስ ስልክ 800 ካሜ

{32} /ጀነራል   አብርሃም ሞገስ ጋጀ፣ ልደታ 800 ካሜ

{33} /ጀነራል   አበባው ሰይድ ይመር፣ ልደታ 800 ካሜ

{34} /ጀነራል   ጀማል ቱፊሳ፣ ንፋስስልክ 800 ካሜ

{35} /ጀነራል   ሞሲሳ ቶሎሳ ገርቦንፋስስልክ 800 ካሜ

{36} /ጀነራል   ዱሬሳ ደገፋ ኤኙኒ፣ቦሌ 800 ካሜ

{37} /ጀነራል   ተስፋዬ ከፍያለው አስፋው፣ ቦሌ 800   

{38} /ጀነራል   እሸቱ መንግስቱ መንገሻ፣ኮልፌ 800ካሜ                      

{39} /ጀነራል   ሁሉአገርሽ ድረስ እንደሻው፣ልደታ 800ካሜ                     

 {40} /ጀነራል   ጌታቸው ሃብታሙ ቸኮል፣ ቂርቆስ 800 ካሜ

{41} /ጀነራል   ዝናቡ አባቦርሳ ሳባጊስ፣ቂርቆስ 800 ካሜ

{42} /ጀነራል   አዘዘው መኮንን አበራ፣ቂርቆስ 800 ካሜ

{43} /ጀነራል   በላይ አየለ ማሞ፣ቂርቆስ፣ 800 ካሜ

{44} /ጀነራል   መላኩ ገላነህ ዘለቀ፣ ቦሌ  800 ካሜ

{45} /ጀነራል   ከበደ ገላው ጅማማ፣ኮልፌ 800 ካሜ

{46} /ጀነራል   ጌታቸው አሊ መሃመድ፣ ኮልፌ  800 ካሜ

{47} /ጀነራል   ካሳ ደምሴ አቡነህ፣  ቂርቆስ 800 ካሜ

{48} /ጀነራል   ሻምበል በየነ ንጉሴ፣ ልደታ  800 ካሜ

{49} /ጀነራል   ኃይሉ መኮንን ምስክር፣ ልደታ 800 ካሜ

{50} /ጀነራል   ተመስገን  ማሎሬ ግዶሬ፣ ቦሌ 800 ካሜ

{51} /ጀነራል   ሓሸም ኢብራሂም አዋሌ፣ ልደታ 800 ካሜ

{52} /ጀነራል   ናስር አህመድ አራስ፣ ልደታ 800 ካሜ

{53} /ጀነራል   ወርቅነህ ጉዴታ በድሉ፣ ልደታ  800 ካሜ

{54} /ጀነራል   መካሻጀምበሬ አምባው፣ልደታ 800 ካሜ

{55} /ጀነራል   ያደቴ አመንቴ ገላን፣ ኮልፌ 800 ካሜ  ………………………………………………(3)

Specter of demolition looms over Addis Ababa’s historic buildings, igniting fears of a vanishing cultural heritage and a deliberate erasure of the city’s past. Balancing the relentless march of progress with the imperative to safeguard architectural treasures is a universal challenge cities face worldwide……..In this critical juncture, Addis Ababa can draw inspiration from the triumphs and tribulations of other nations. Exploring innovative strategies like adaptive reuse, robust preservation regulations, and meaningful community involvement can ensure the city’s architectural legacy thrives amidst the winds of change. It’s a delicate dance between preservation and progress, where Addis Ababa can script its unique narrative of harmonizing tradition and modernization.

የአዲስ አበባን ጥንታዊና ታሪካዊ ህንፃዎችና ሥፍራዎችየማፍረስ ዘመቻ ቅርስና ውርሰስ ኃብቶችን የማጥፋትና ሆን ብሎ የከተማዋን ጥንታዊ የማንነት ታሪክ ማውደም ተልእኮ አለው፡፡ ጥንታዊውንና ዘመናዊውን የኪነ-ህንፃዎች ኃብት ለሚቀጥለው ትውልድ አዛምዶ ማስተላለፍ የዓለም አቀፍ የከተሞች እድገትና ተግዳሮቶች  ፈታኝ ጥያቄዎች ናቸው፡፡ የአዶስ አበባም ፈተናዋ የድሮውን ከአዲሱ የሥነ-ህንጻ አዋህዶ ፈር ቀዳጅ ስትራቴጂ አውጥቶ ዳግም የመሬቱን አጠቃቀም የቅርሥ ጥበቃውን በህዝብ ተሳትፎና ምክር፣ ጥንታዊውንና ዘመናዊውን የኪነ-ህንፃዎች ኃብት አስታርቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ ነው፡፡

ምንጭ

(1) A City Without Its Past Addis Ababa’s Transformation Puts Heritage at Stake/ 11th Year • September 2023 • No. 121 EBR

(2) ፈርሰን ሳናልቅ እንድረስየሐኪም ወርቅነህ እሸቴ ቤት የዓለም አቀፍ ታሪካችን ሙዚየም ነውሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best And Reliable News Source In Ethiopia/በሱራፌል ወንድሙ (/)/ቀን: March 27, 2024

(3) ቅጥረኛ የአብይ አህመድ ጄነራሎች ለሚያፈሱት የአማራና የሌሎች ኢትዮጵያውያን ደም የክፍያቸው መጠን ጨምሯልአንዳርጋቸው ጽጌ/ SEPTEMBER 23, 2023

Filed in: Amharic