የኢትዮጲስ ጋዜጠኛ ምሥጋን ጌታቸው እና አዳም ውግጅራ ፤ ትላንት ነሃሴ 3/2011 የችሎት ውሎ ለመዘገብ በተገኙበት ፍርድ ቤት ፖሊስ ይዞ ያስራቸዋል።
እነኚህ ጋዜጠኞች በችሎት ለመታደመ እና ለመዘገብ ከተገኙበት ቦታ የያዛቸው ፖሊስ ፤ አንድ ቀን አስሮ አሳድሮ በማግስቱ ፤ በፀረ-ሽብር ህጉ በመወንጀል ፍርድ ቤት አቅርቦ የ 28ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቆባቸዋል።
እርግጥ ነው ፤ እንዲህ ያለው ነገር የሚያመላክተው አስቀድሞ በግፍ የታሰሩት የህሊና እስረኞች ፤ የቀረበባቸው የሽብር ክስ ምን ያህል የሐሰት እንደሆነ የሚያሳብቅ ነው።