>
5:21 pm - Sunday July 20, 0380

"ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አይን እየገለጠችላቸው ነው....!!!" (የኢራን ወታደራዊ አዛዥ ጀነራል አሽራፍ  ናስር አብደል ቀኒ)

“ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አይን እየገለጠችላቸው ነው….!!!”

የኢራን ወታደራዊ አዛዥ ጀነራል አሽራፍ  ናስር አብደል ቀኒ

ወቅታዊ የኢትዮጵያን ጉዳይ በማስመልከት ለ PressTV በሰጡት መግለጫ
*… ኢራን ለኢትዮጵያ ህግ ማስከበር ዘመቻ ሁለት (2) ዘመናዊ ድሮኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች ሲሉ ገልፀዋል
 “ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን አይን እየገለጠችላቸው ነው በአሜሪካ ሴራ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ወደ ድንጋይ ዘመን ተመልሰዋል ይሄ ሁሉ ሲሆን ኢራን መንግስትና ህዝብ በብቸኝነት ለሀገራቶቹ መንግስት ሲከላከልና የአሜሪካን ጣልቃ ገብነት ስንቃወም ቆይተናል
ሆኖም እኛን አድማጭ አጥተን እና በአለማቀፉ ማህበረሰብ በሽብርተኝነት እንድንያዝና በፀጥታው ምክር ቤት ተደጋጋሚ ማዕቀብ ሲጣሉብን ከርመናል  ሰሚ ግን አላገኘንም
 የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ተደማጭነትና ከቀድሞ አባቶቻቸው የወረሱት ለቅኝ ገዢዎች አንገዛም ባይነት ታሪካቸው ለዛሬው የአሜሪካ ቅሌት እንዲጋለጥ ጠቅሟታል ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ የራሷን ብቻ ሳይሆን ብዙ የታፈኑ የአለም ሀገራትን እኛን ጨምሮ ድምፃችን እንዲሰማ ምክንያት ሆናለች
  አሁን የቅኝ ገዚ እሳቤ ያልተላቀቀችሁ ሀገረ አሜሪካ ዲፕሎማሲዋ አፈር በልቷል ቀኗም እየጨለመ ነው በአለም ላይ ካሉት 171ሀገራት  100ና ከዚያ በላይ የሆኑት ከኢትዮጵያ ጎን ቆመው አሜሪካንን እያወገዙ ነው
 ኢትዮጵያ የሁላችንንም በደል ገልፃለች ለዚህም እናመሰግናታለን ! ከጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ ጋርም አብረን ለመዝመት ፈቃደኞች ነን
ከዚህ በተጨማሪም ኢራን ለኢትዮጵያ ህግ ማስከበር ዘመቻ ሁለት (2) ዘመናዊ ድሮኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች ሲሉ ገልፀዋል
እኛም አመስግነናል!
ብሌን ሚድያ ሀውስ
Filed in: Amharic