>

የእግዚአብሔር ቁጣ በሁሉ ኢትዮጵያን በደፈሩ ላይ መዝነቡን ይቀጥላል። (መምህር ዘመድኩን በቀለ)

የእግዚአብሔር ቁጣ በሁሉ ኢትዮጵያን በደፈሩ ላይ መዝነቡን ይቀጥላል።

በመምህር ዘመድኩን በቀለ

“ርዕሰ አንቀጽ” 

“…ከፊታችን ባለው ጊዜ ሩቅ ባልሆነ ጊዜ ድብልቅልቃቸው የሚወጣውን፣ በመቅሰፍት ታጥበው፣ ተጨምቀው፣ ተበጥረው፣ ተፈትገው፣ ተወቅጠው፣ የሚከኩትን የከበረውን የጵጵስና ማእረግ ያዋረዱ፣ ያረከሱ ዘረኞችን፣ ዘማውያን፣ የቆብ ስር የወንድ መነኩሴ ጋለሞቶችን አጀንዳ አድርጎ መጯጯሁ ምንም ጥቅም የለውም። ሁላቸውም አንድ ናቸው። ቀደም ሲል በብዙ ተደክሞበት በብዙ ሴራ ነው ከዚህ ላይ የደረሱት። እናም እንደ እንግዳ ደራሽ፣ እንደ ውኃ ፈሳሽ ጎርፍ ሆኖ እለት፣ ድንገት የተከሰተ አይደለም። ይሄ ከደርግ መምጣት ጀምሮ ሲለፋበት፣ ሲደከምበት ቆይቶ፣ የህወሓት መምጣት አቡኩቶት፣ አቆሽሾት፣ የአቢይ አገዛዝ ደግሞ አግማምቶ፣ አጠንብቶት ለቆት ስላየን ነው እንጂ ጉዳዩ የቆየ ነው። ከፋሽስት መውደም፣ ከነጮቹ መሸነፍ ዘመን በኋላ የተወሰነ ነገር ነው። የቆየ ነው። ግን አይሳካም።

“…ኢትዮጵያን ለሚያፈርሱ ሁሉ በዘመናቸው ተባባሪ የሆኑት እነዚህ ጎረምሳ፣ ጎረምሳ ብቻ ሳይሆን ሰነፍ የድሀ ልጆች ጥርቅም የሆኑ ሠርቶ መብላት ስላልቻሉ በአባትነት ስም ተወዝፈ፣ እየማገጡ፣ እያማረጡም፣ ለፖለቲካው ኮንዶም ሆኖ በማገልገል በቋመጡ ቁጭ ብሎ መብላትን ምርጫቸው ባደረጉ፣ ለሃይማኖታቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ቅድሚያ ለሰጡ፣ ለራሳቸው የግል ምቾት እንጂ ለበጎቹ ደንታ ለሌላቸው፣ አብዛኞቹ የወንድ አራስ ወላድ ለሆኑ ነውረኛ የመነኮስ ጥርቅም ቦታም ጆርም አትስጧቸው። ጊዜአችሁንም በእነሱ የኮተት ዜና ላይም አታጥፉ። ልክ ሃገር አፍራሾች ጉልበት ጊዜ አግኝተው ሁሉን እንዳፈራረሱት ሃገር ገንቢዎችም ሲመጡ ይሄን የቆሻሻ ክምር መዓት ከቤተ ክህነቱም ከቤተ መንግሥቱም ሁሉ አፅድተው እንደ ጥንቱ እንደቀድሞው ውብም አንድም ያደርጉታል።

“…በአቡነ ማትያስ የሚመራውም የአዲስ አበባው ሲኖዶስም የሠራው ልክ አይደለም። በእቅድ ነው ቀኖና የተጣሰው። የትግራዩም ልክ አይደለም በ1970ዎቹ መጀመሪያ የተመሠረተ የጥፋት ፕሮጀክት ነው አሁን የቀጠለው። የኦሮሚያዎቹም ልክ አልነበረም። የትግሬዎቹ ፕሮጀክት ሆኖ ቆይቶ ኦሮሞዎቹን እንደ አይጥ ከሞከሩባቸው በኋላ የተገለጠ ነበር። አሁንም ከትግራዮቹ ሺ ሞት በኋላ ጥፋቱ እንደ አዲስ ይቀጥላል። በተለይ የአራት ኪሎው ዋነኛ አጥፊ ሲኖዶስ የአክሱሞቹን በፍጥነት ተሰብስቦ ካላወገዘ በቀር ኦሮሞዎቹ አሁን በእነ ጃዋር በኩል እንደ አዲስ ሄጵ በማለት በእስላሙና በጴንጤው የብልፅግና ኦሮሞ አማካኝነት ድብልቅልቁን ያወጡታል። በተለይ ሲኖዶሱ ተሰብስቦ ካለዋገዘ ቀውጢው ቀላል አይምስለህ የሚሆነው። ከዚያ የእብድ ትርምስ ነው በኢትዮጵያ የሚፈጠረው። በጎጃምም ቆጋ ተክለሃይማኖት ፓትርያርክ መርጦ ያስቀመጠው የቅባት ቡድንም አሁን የአክሱሙን ሹመት ተከትሎ በቀጥታ ሌላ ብዛት ያላቸው ጳጳሳት ወደ መምረጡ እየገባ ነው የሚል ወሬም አለ። ሆኖም ግን ሁሉም ይደፈርሳል ነገርግን ደግሞ ሁሉም ነገር በጊዜው ይጠራል። ምእመናንን ግን በወንድ ጥጋበኛ ቅሌታም የሽማግሌና የጎረምሶች ውንብድና የቦዘኔ ተግባር ተደናግጣችሁ ስፍራችሁን እንዳትለቁ።

“…ታዲያ ስማኝ ይሄ ሁሉ የሚስተካከለው የዐማራ ፖለቲካ ሲስተካከል ብቻ ነው። ይሄን በድፍረት ስናገር እኔ ዘመዴ የምቀልድ ይመስላችኋል። ማርያም ምስክሬ ናት አዛኜን ነው የምላችሁ እውነቱ እሱ ብቻ ነው። ይሄ ሁሉ ፈተና እኮ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈሰው በዐማራ ምክንያት ነው። ትግሬም ኦሮሞም ነን የሚሉ አካላት የሚከሱት ዐማራውን ነው አይደል? እናም በዐማራ ምክንያት ከሆነ ይሄ ሁሉ ፍዳ የሚደርስብን ዐማራው የፈጀውን ጊዜ ፈጅቶ፣ የፈጀውን ዘመን፣ ሃብትና ሕይወትም ፈጅቶ ዳግም ወደ ሥልጣን መጥቶ የግድ ይሄን ቆሻሻ ማስተካከል አለበት። አይሆንም ብሎ የሚያስብ እንዳይኖር። ጉዳዩ ወደድክም ጠላህም የዘርና የሃይማኖት ነው። ይሄ ያልተገለጠለት ዐማራም፣ ኢትዮጵያዊም ካለ እንጭጭ፣ እንጭቅ፣ እምቦጫም ጥርብ ሰገጤ መቶ ኪሎ ፋራ ብቻ ነው መሆን ያለበት።

“…ይልቅ ሌላ ዐማራውን የሚያሳስበው እና ሊጠነቀቀው የሚገባውን ነገር ልተንፍስለት። ብዙዎቻችሁ ልትንጫጩ ትችላላችሁ። እሱ የራሳችሁ ጉዳይ ነው። ለምን በአናትህ አትተከልም። ወደዳችሁም ጠላችሁም ዐማራ አቶ ዮሐንስ ቧያለው የሚባለውን መርዘኛ ሰውዬ መጠንቀቅ አለበት ባይ ነኝ። ቧያለውን ብቻ አይደለም። እነ ገዱ አንዳርጋቸውን፣ እነ ዶር ደሳለኝ ጫኔና እነ አቶ ክርስቲያን ታደለን ጭምር በንስር ዓይን ዓይቶ መጠንቀቅ አለበት ባይ ነኝ። ክሪስና ጫኔ በፓርላማ ተቀምጠው አቢይ አሕመድን በመተንኮስ አቢይ አፉን እንዲከፍት እያደረጉ የእንደራሴነት ደሞዛቸውን እየላፉ ዐማራን በጮማ ወሬ ደስታ ራሱን በራሱ እያረካ ሚስት ሳያገባ፣ ዘር ሳይተካ ተጎልቶ እንዲኖር የሚያደርጉ ማስተርቤተሮች ናቸው የሚመስሉኝ። አቶ ገዱ አንዳርጋቸውም እንደዚያው ነው። የተጣላ መስሎ ፀደይ ባንክን 300 ሺ ብር ደሞዝ እየላፈ ለክፉ ቀን አቢይና ደመቀ ያዘጋጁት ዘመሚት ነው። አቶ ዮሐንስ ቧ ያለው ግን ሲበዛ በተጠና መልኩ በሚገርም ጥበብ ዐማራን ለማደንዘዝ የታጨ ክፉ አጫዋች፣ አደንዛዥ አደገኛ መርዛም የሳር ውስጥ እባብም የጭቃ ውስጥ እሾህም የሆነ ሰው ነው የሚመስለኝ። መምሰል ብቻም አይደለም።

“…ሲጀመር አቶ ዮሐንስ ቧያለው ጀነራል አሳምነው ጽጌን ያስበላ፣ ጓዶቹን እነ ዶር አምባቸውን ያስገደለ፣ የፍርድ፣ የፍትሕ ጊዜ የእውነት ዘመን ሲመጣ ከነ ላቀ አያሌው፣ ከእነ አገኘሁ ተሻገር፣ ከእነ አቶ አብርሃም ከእነ መላኩ አለበል፣ ከአሰማኸኝ ጋር እኩል የሚጠየቅ ለፍርድም የሚቀርብ አተላ የሆነ ሰው ነው። በቀደሙት ጊዜያት በየመግለጫው እየቀረበ ጄነራል አሳምነው ጽጌን ሲወቅስ የኖረ ሰው ነው። እሱ ብቻ አይደለም ይሄ አሁን ጥይት በሰውነቱ ገብቶ ህክምና የተከለከለው ጄነራል ራሱ አሳምነውን ሲሰድብ የነበረ ሰው ነው። አቶ አበረ አዳሙ አሳምነው ጽጌን እብድ ነው ብሎ በአቢይ ቢሾምም በመርዝ ነው የተወገደው። እናም አሁንም ይሄ አሽቄ የድሮ አራዳ ዮሐንስ ቧያለው ከአቢይ አሕመድ ጋር ተመሳጥሮ፣ ከዐማራ ምክርቤት ጋር በመተባባር አዲስ ምርጥ የማደንዘዣ ድራማ እንዲተውን ተደርጎ ይምበጫበጫል። ጥፋ በለው።

“…ስሙኝማ አቶ ዮሐንስ ቧያለው አሁንም የዐማራ ብልፅግና አባል ነው። ደሞዙን እየላፈ ፏ ብሎ የሚኖር ብልፅግና ነው። ልብበሉ እንዲህ እየለፈለፈ አንዳች ነገር አያደርጉትም። የብልፅግና ማእከላዊ ኮሚቴ የሚያወርድለትን የመጫወቻ ካርታ ጊዜና ሰዓት ጠብቆ የጨዋታውን ሕግ ተከትሎ በጥንቃቄ ዐማሮች ዐይንና ጆሮ ላይ በአግባቡ እንዲተውን የተመደበ ይሁዳ የሆነ ግለሰብ ነው። ሲጀመር ከሌሎች የምክርቤቱ አባላት በተለየ መልኩ የዮሐንስ ቧያለው ዲስኩር ብቻ ለምን ሙሉው እንዲቀረጽ፣ ከተቀረጸም በኋላ ደግሞ ከመሳይ መኮንን አንከር ሚዲያ ለጥቆ ግራ እያጋባኝ እየመጣ ባለው በወንድማችን በአበባ በለው አዲስ ድምጽ ሚዲያ ላይ ተልኮ ዓለሙ ሁሉ እንዲያዳምጠው ተደረገ ብዬም ራሴን እጠይቃለሁ? አቤ አበበ በለው ከእነ ፕሮፍ ትንግርቱ ጋር ለምን እንዲቀናጅ ተደረገ? ኢትዮ 360 ዎች ሳያስቡት በአርቲስት ሽመልስ አማካኝነት በየዋህነት የብአዴን ኮተቶች መጠለያ ታዛ እንዲሆኑስ ለምን ተመረጠ? ለምሳሌ አቶ ልደቱ አያሌው የአቢይ አገዛዝ “አሸባሪ” ካለው በኋላ በትግሬ፣ በኦሮሞና በጥቃቅን ዩቲዩበሮች፣ ቲክታከሮች ቤት ሳይቀር እየገባ ከመበጥረቅ በቀር ኢትዮ 360 ላይ ቀርቦም፣ ደውሎላቸውም አያውቅም። እናም እነ ሀብታሙ አያሌውም በቀኝ አዙር የብአዴን ሴል ተጠልፈው እንዳይወድቁ ሊጠነቀቁ ይገባል።

በተለይ ገንዘብ ያጡ በመሰላቸው ጊዜ በአላሙዲን፣ በአቶ አብነትም በኩል ከጀርባ ኢትዮ 360 ዎችን ለማፍረክረክ እየተደከመ መሆኑን ዐውቀለሁ። ምናላቸው ስማቸውን ያናገረው የአላሙዲ ሰው በመጀመሪያ እኔ ዘመድኩን በቀለን ነው ያናገረኝ። ሂድ ጥፋ፣ አንተም ገንዘብህም ገደል ግቡ ያልኩት ሰው ነው ኢትዮ 360 በጀርባ ገብቶ ስለ አላሙዲ እንዲዘገብና ፈንድ እንዲለቀቅላቸው አደርጋለሁ ብሎ የሚያንበጨብጫቸው። ወዳጄ የንስር አይን የሚያስፈልገው አሁን ነው። የተገኘው መረጃ ሁሉ አይነገርም። እንደ ዓሣ በብልሃት መብላት አስፈላጊ ነው።

“…እኔ ዘመዴ በድብቅ ወጣ የተባለውን የአቶ ዮሐንስን የምክርቤት በመርዝ የተለወሰ መርዘኛ ንግግር መላልሼ ሰምቼዋለሁ። እሱን ብቻ ሳይሆን ከምክር ቤት ከወጣ በኋላ ከሆነ ሰው ጋር በስልክ ሲበጠረቅ የተቀዳውንም የስልክ ንግግሩንም አድምጬዋለሁ። ከምር አቶ ዮሐንስ ቧያለው የያዘው የዐማራን ትግል ዳግም የመጥለፍ አካሄድ ነው። እናም ከወዱሁ ተነቅቶብሃል አርፈህ ተቀመጥ ሊባልም ይገባል? ኮተታም ብአዴን። አቶ ቧያለው በምክርቤቱ የተናገራቸው በሙሉ በዐማራ ላይ ይደርሳል ያላቸው ነገሮች እኛ ዘወትር ከምንናገረው ምኑ ነው የሚለየው? በቀቀናም። በዐማራ ላይ እየደረሰ ነው ያላቸው ግፎች በሙሉ አብዛኞቹ እኮ እርሱ ራሱ ሥልጣን ላይ እያለ በእሱ አመራር ሰጪነት የደረሱ ጥፋቶች ናቸው። ዐማራን ዝቅ አድርጎ ሲሳደብ የነበረ ልፋጫም ብአዴን አሁን የዐማራው ትግል መስመር እየያዘ ሲመጣ ከየት አባቱ መጥቶ ነው አዛኝ ቅቤ አንጓች የሚሆነው?  እነ ዮሐንስ እነ ገዱ አሮጌ አቁማዳቸውን ይዘው አዲሱን ወይን ሊያፈሱት ከዘራቸውን ይዘው እየተንገዳገዱና እየተወላከፉ፣ በአለቀ ጥርሳቸው ሾልኮ በድዳቸው በኩል ላያችን ላይ በሚረጩት ለሃጭ ታጅበው፣ ከነዳይፐራቸው እየገሙ፣ እየከረፉ፣ እየጠነቡ የዐማራውን ባያጠነቡት ትግሉንም ለመጥለፍ ባይታትሩ መልካም ነው። እናም ዐማራ ሆይ ይሄን ኮተታም ብአዴን ጥፋበለው። በአሮጌ ወይን አዲስ አቁማዳ አይቀመጥም በለው።

“…ዮሐንስ ቧያለው ምንድነው ያለው? 4ኪሎን አስቦ የተነሣውን የዐማራ ፋኖ በድርድር ሰበብ ጉዞውን እንዲገታ ማድረግ ነው የፈለገው። ለድርድሩ እንዲያውም እኔ ራሴ ፕሮፖዛል አዘጋጃለሁ ነው የሚለው። ተመልከቱ የብልፅግና አባሉ ቧያለው መንግሥት ከፋኖ ጋር የሚያደርገውን ድርድር እያዘጋጀሁ ነው የሚለው። ከዚህም አልፎ በሽምግልናው የማይስማሙ ፋኖዎች ካሉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል ነው የሚለው ቧያለው። ይሄ ታዲያ ከአበባው ታደሰ፣ ከብራኑ ጁላ፣ ከአቢይ አሕመድ አባባል በምን ይለያል? እናም ዐማራ በእንደ ዮሐንስ ቧያለው ያለ አሮጌ የብአዴን አራዳ ገገማ ሰገጤ እንዳይጭበረበር ሊጠነቀቅ ይገባል። ለአዲሱ የዐማራ ፖለቲካ ብአዴን የሆነ ሰው መፍትሄ ሊሆነው አይችልም። የማከብራቸው አቶ ክርስቲያን ታደለ እና ዶክተር ደሳለኝ ጫኔም የዚሁ ቫይረስ ተጠቂ ስለሆኑ እነሱን እየሰሙ ራስን በራስ ማርካት ለጤናችሁ ጥሩ አይመጣም እና ሳታቀርቧቸው በሩቅ እንደ አጫዋች ፈን እየያዛችሁባቸው ብታስቀምጡአቸው መልካም ነው ባይ ነኝ። ከዮሐንስ ቧያለው ጋር በውስጥ መስመር ንግግር፣ ድርድር የጀመራችሁም የፋኖ አመራሮች በአስቸኳይ ድርድር ንግግሩን አቁሙ። የምን በቱርጁማን ንግግር፣ ድርድር ነው። አልያ ትበላላችሁ ነግርቻለሁ። አከተመ።

“…ይልቅ ሌላ ጮማ የሆነ የጥንቃቄ ወሬ ልንገርህማ። አሁን ሩቅ ባልተባለ ጊዜ አርማጌዶን የሆነ ጦርነት በጎንደር በኩል ይፈነዳል። ቀድሞ የገባው፣ የነቃ ዐማራም ይሄን አርማጌዶን ተዘጋጅቶ እየጠበቀ ነው። አደጋው የሚጀምረው ከጎንደር ይሁን እንጂ ራያ፣ ጠለምት፣ ወሎ፣ ሸዋ፣ ጎጃምም አይቀርለትም። አሜሪካኖቹ መጀመሪያ ራያን ሄደው አይተውታል። የራያን ዐማራም ገምግመው ተመልሰዋል። ህወሓቶች በአሜሪካ ኦህዴድና ኦነግ በአዳማ መክረው ሁሉን ጨርሰዋል። ሁላቸውም ጠላታቸው ዐማራው መሆኑን አስምረውበታል። አሁንም አሜሪካኖቹ መልሰው ሰሞኑን ጎንደርና ባሕርዳር ለመሄድ ዝግጅታቸውን መጨረሳቸውን በይፋ አሳውቀዋል። ጎንደር የሚሄዱት የፋሲልን ግንብ ሊጎበኙ አይደለም። ባሕርዳርም የሚሄዱት በጣና ሐይቅ ሽር ብትን ሊሉም አይደለም። ይሰመርበት…

“…የፋኖ ትግል ሰብሮ ከወጣ አሜሪካኖቹ አቢይ አሕመድን ወገብ ዛላውን ሰብረው በለውጥ ስም አስወግደው የፋኖን ግስጋሴ ለመግታት ይሠራሉ። ለአሜሪካ እስከሠራህላት ድረስ አምባገነን፣ ጨፍጫፊም ብትሆን ትከላከልልሃለች፣ ሌላ ኃይል ከገጠማት ደግሞ እንደ ወያኔ በካልቾ ጠልዛ ደደቢት ትወሽቅሃለች፣ ወይም እንደ ሌሎቹ ገላ ቱቦ ለቱቦ ታስጎትትሃለች። ፋኖ ሰንሰለቱን አስኳሉን ሰብሮ የማይወጣ ከሆነ ደግሞ በዚሁ መሃይም ራስ ወዳድ የህዳር አህያ ተጠቅመው ዐማራን የማፍረስ ትግላቸውን፣ የተጻፈ ዕቅዳቸውን ማስፈጸሙን ይቀጥላሉ። ወሳኙ የዐማራው ጥንካሬ፣ ፍጥነት እና ጀብዱ፣ ድልም ብቻ ነው።

“…አሁን የአብይ አሕመድ የኦሮሙማ ጦር በጠለምት ዙሪያ መስፈር ጀምሯል። በራያ ማዶውንም እንደዚያው፣ በወልቃይትም በጠገዴ ዙሪያ በትግሬ ወገን በኩል ሆኖ ጦሩ እንደ ጉድ እየተከማቸ መሆኑ እየተነገረ ነው። በጎጃም፣ በሰሜንሸዋ፣ በወሎም እንዲሁ ተከማችቶ ገብቷል። በጠለምት እንዲያውም አላስችል ያለው መታገስ ያቃተው የትግሬ ጦር መከላከያ አለልኝ ብሎ የአካባቢው ፋኖና ፖሊስ ላይ ጦርነት ከፍቶ በ30 ደቂቃ ውስጥ ብትንትኑ ወጥቷል። መከላከያውም አብሮ ነው የፈረጠጠው። ሆኖም ግን የመከላከያው ባለሥልጣናት የዐማራን አስተዳዳሪዎች ስብሰባ ጠርተው ዐማራን በ24 ሰዓት መበተን እንደሚችሉ መናገራቸውን በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ሲቀርብ ሰምተነዋል።

“…የአቢይ አሕመድ አገዛዝ የጠየቀውን ቢልዮን ዶላሮች ነጮቹ እንዲለቁለት በባሌም ሆነ በቦሌ ብሎ ወልቃይት ጠገዴን፣ ጠለምትናንና ራያን ለትግራይ መስጠት አለበት። ለዚህም ደግሞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምሯል። የትግሬ ጦር ከመከላከያ ጋር አንድ ሆኗል። አንዳንድ ቦታ መከላከያውን የትግሬ ተሸናፊ ጀነራሎች መምራት ሁላ ጀምረዋል። ሥልጠናም በጋራ ነው እየወሰዱ ያሉት። ሲጋራም አንድ ለሁለት ነው የሚያጨሱት። ከፊታቸው እንቅፋት ሊሆን የሚችል ኃይልም እንዳይኖር ብለው በበድኑ ብአዴን ተባባሪነት የዐማራን ልዩ ኃይል አፍርሰዋል። የቀረውን ፋኖም ለመደምሰስ እየተላላጡ ነው። ሚኒሻው እንኳ ለዘር እንዳይተርፍ ከፋኖ ጋር እያታኮሱ ዐማራን በሃላል ለማውደም በጥምር እየሠሩ ነው።

“…ጎንደር ዝግጅትም፣ ውጥረትም ላይ ናት። በወልቃይት ዐማራው እየሰለጠነም፣ እየታጠቀም ነው። በመተማ ቋራ አካባቢ ደግሞ በቅማንት ስም ትግሬ ያሰማራው ቡድን ዐማራ እያገተ፣ ገበሬ እየገደለ፣ በዐማራ ሲመከት መከላከያ ካምፕ ሮጦ የሚገባ ኃይል በአቢይ አገዛዝ እየተደራጀ ነው። የእነ ሰማ ጥሩነህ ቡድንም የክልሉን ፕሬዘዳንት አቶ ይልቃልን በማስወገድ ዐማራን በመረከብ የአገው ሸንጎ ብለው የፈጠሩትን ቡድን ወደፊት ለማምጣት እየታተሩ ነው። ሰማጥሩነህና ደጀኔ የይልቃል ገዳዮች ናቸው ተብሏል። ዐማራውን በዙሪያው እንደ ብራና ቆዳ በተለያየ ችግር በመወጠር በብዙ የሚደክሙ ኃይላትም እንደ አሸን ተፈጥረዋል። የተከበሩ ስመጥር ፋኖዎችም በገንዘብ ተጠልፈው የእነ እስክንድርን ትግል ከመጥለፍ፣ እስክንድርን ራሱ ለመግደል ከብአዴን ጋር መዶለታቸውም ወፎቼ እየተናገሩ ነው። የሕዝባዊ ኃይሉ መቋቋም የገቢ ምንጫቸውን ያደረቀባቸው አውርቶ አደር ፋኖ ተብዬዎች ልክ እነ አሳምነውን በበሉበት መንገድ እስክንድርንም በልተው ትግሉ ላይ ውኃ ለመቸለስ መዘጋጀታቸው  ነው የሚነገረው። በእስክንድር ብስጭታቸውን መደበቅ ያቃታቸው ዐማሮችን ማየት ያስቃል። እናም ዐማራ ለማይቀርልህ አርማጌዶን ተዘጋጅ እንጂ በዮሐንስ ቧያለው፣ በክሪስ እና በደሱ ዲስኩር ማስተርቤት አታድርግ። ከነቃህ ታሸነፋለህ፣ ካልነቃህ መሸነፍ አይደለም ከምድረገጽ ትጠፋታለህ። ይኸው ነው።

“…ለዐማራ የመጨረሻው ምክሬ ይህ ነው።  በሚቀጥለው ዓመት በዐማራም በኢትዮጵያም የእህል ምርት ይቀንሳል። ይሄ ሆን ተብሎ በጥናት የተፈጸመ ነው። ዐማራው ከራብም፣ ከቸነፈርም፣ ከበሽታም፣ ከሱዳንም፣ ከጉምዝም፣ ከህወሓትም፣ ከኦነግም፣ ከብልፅግና ከመከላከያም በባዶ ሆድህ እንደትገጥም የተሠራ ዕቅድ ነው። ይሄንን ችግር ለማለፍ ደግሞ በማዳበሪያ እገዛ ቡኩንታል የምታፍሰው እህል ቢቀርብህም አንድም ቁና ቢሆን ምርት ብታገኝ መልካም ነውና ባለህ መሬት ላይ ጠበል፣ እምነት፣ እበት፣ ኩበትም እያደረግክ አሁኑኑ ዘር ዝራ፣ በረከቱን እንዲያወርድልህ ጸልይ፣ አምርት።

“…በሚቀጥለው ዓመት ጤፍ ለዐማራ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ሁሉ የሜርኩሪ ያህል ሊወደድ፣ ሊጠፋ ይችላል። እናም ዛሬ የዐማራ ገበሬ ሰልፍ ወጥቶ የማዳበሪያ ያለህ ሲል ቆሞ ሲስቅ የነበረ ሁሉ መግቢያ መውጪያ አጥቶ ሲንከራተት ለማየት ጠንቋይ ቀላቢ መሆን አይጠበቅም። እናም ዐማራ ሆይ ለጥቂት ጊዜ የእህል ቁጠባ ብታደርግ፣ ድግስ፣ ተዝካር፣ ቅጥ ያጣ ግብዣ ብታቆም መልካም ነው። ደግሞም ጾም መጾም ከአሁኑ ተለማመድ፣ እንደ አሳማ ሌሊት ተነሥተህ አታመንዥክ። እህል ከአሁኑ እንደ ትግሬና እንደ ኦሮሞ በጎተራም፣ በመሬት ውስጥ ቀብረህ ብታዘጋጅ መልካም ነው። እየመከርኩህ ነው።

“…በዐማራ ክልል የምትገኙ ገዳማት እና አድባራት ታቦታትን ጨምሮ ከወዲሁ ደብቁ፣ ሰውሩ። በመጪው ጊዜ ዋነኛው የጦር ዐውድማ የሚሆኑት ጥንታውያኑ ገዳማት እና አድባራት ስለሆኑ የብራና መጻሕፍትን፣ ታላላቅ ቅርሶችን፣ ሊቃውንቱን ሁሉ ከወዲሁ ልክ እንደ ታቦተ ጽዮን ብትሰውሩ መልካም ነው። ታቦተ ጽዮንን የሰሜኑ ጦርነት ገና ሳይጀመር አባቶቻችን እንዳሸሿት፣ እንደሰወሯት ሁሉ እናንተም ከወዲሁ ቅርሶቻችሁን ሰውሩ። ማዕበል ወጀቡ ሲያልፍ ይወጣሉ።

“…ሌላው ለሕዳሴ ግድብ፣ ለሃገር መከላከያ ሠራዊት ተብሎ በአቢይ አሕመድ በቀጣይ በእጅህ የቀረውን ገንዘብ ለመሰብሰብ ዘመቻ ይጀመራል። ልክ ወሎ ደሴ ላይ የሆኑ የብልፅግና የኦርቶዶክስ መነኩሴ ካድሬዎች ለደሴ ከተማ ልማት ብለው ግማሽ ሚልዮን ብር ሰብስበው እንዲሰጡ እንደተደረገው ማለት ነው። በግብር፣ በታክስ የደቀቀው፣ በመዋጮም የፎዘው ዐማራ፣ አሁን ደግሞ ለመከላከያ ሠራዊቱ መዋጮ ብለው የቀረውን እጅህ ላይ ያለውን ገንዘብ ሊሰበስቡ ነው እና አስብበት።

“…የዶር ዳኛቸው አሰፋንም በራሱ እመጣበታለሁ። ዐማራ በተለይ ጎንደሮች ትጠነቀቁት ዘንድ እጽፍላችኋለሁ። የአሜሪካንንም እንቅስቃሴ በደንብ ታጤኑት ዘንድም እመክራችኋለሁ። ባይመለከታችሁም ልንገራችሁ። ተመልከቱ ዓድዌዎቹ እነ ደጽዮን፣ እነ ፈትለወርቅና ሌሎች 5 ወያኔዎች ልክ እንደ አቦይ ስብሃት ወደ አሜሪካ ለመውጣት ተንጋግተው አሜሪካ ኤምባሲ ሄደው ነበር። አሜሪካም አይ ለዓድዋዎች ቪዛ አንሰጥም ብለው መልሰዋቸዋል። ነገር ግን ባለፈው ለራያ ዐማራው ጻድቃን፣ አሁን ደግሞ ለራያ ዐማሮቹ ለጌታቾና አብረውት ለሚጓዙ 2 ሰዎች አሜሪካ እልል ብላ ቪዛ ሰጥታ ጌች አሜሪካ ነው ገብቷል።

“…አሜሪካ በህውሓትም በአብአይም ተስፋ መቁረጧን ተከትሎ ወያኔዎች እንደ ፃድቃን ከኢትዮጲያ አምልጠው ለመውጣት ቢሟሟቱም አሜሪካ ላሽ በሉ ብላቸዋለች። በዚህ የተበሳጩት አድዋዎቹ በአስቸኳይ ሃገር ማተራመስ አለብን ብለው ሽማግሌ ገተቶቹን የትግሬ ጳጳሳት አካልበው ሸርሙጣ ጳጳሳት እንዲሾሙ አድርገዋል። በቀጣይ የሚበላ የሚጠጣ ያጣው፣ ለዐማራ መግደያ ያዘጋጁትና ያሰለጠኑት አሁን በጠራራ ፀሐይ በጩቤ የሚዘላዘለው፣ ሴት የሚደፍረው፣ መረን የለቀው ወጣት እያንዳንዳቸውን የዓድዋ ባለሥልጣናትን በየቤታቸው እየሄደ ዘልዝሎ ይበላቸዋል። ቱ…ምንአለ ዘመዴ በሉኝ።

“…ደሞዝ መክፈል የማይችል ክልል፣ የሚበላው የሌለው ክልል፣ ከኢትዮጲያ ከመቀበል ውጪ አንዲት ሲኒ አምርቶ ለሀገራችን ገበያ ጂዲፒ የማያቀርብ የማያዋጣ ክልል፣  ኤጲስ ቆጶስ ጳጳስ ሾመ አልሾመ ብለህ አዳሜና ሔዋኔ ጊዜህን አታባክን፣ ከማን ካዝና ተወስዶ ለሸርሙጣ ለጋለሞታ ጳጳስ ተብዬ የጨረቃ ጳጳሳት እንደሚከፍል እናያለን። ወደ ዐማራም ለውጊያ ከመጣ ጠብቆ ማደባያት ነው። እዚያው ትግሬም ከቀረ እርስ በእርሱ ተባልቶ ማለቁ ነው። የእግዚአብሔር ቁጣ በሁሉ ኢትዮጵያን በደፈሩ ላይ መዝነቡን ይቀጥላል።

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው

Filed in: Amharic