‹‹ካልአን ፍጥረታት››

ከይኄይስ እውነቱ

‹‹ካልእ ፍጥረት በሃይማኖት የትርጓሜ መጻሕፍትና ባንዳንድ ባህላዊ ትረካዎች እንደምናነበው የሰው እና የአውሬ መልክ ያለው ልዩ ፍጥረት ነው፡፡ ሰበድአትበመባልም ይታወቃል፡፡ ካልእ የሚለው ቃል በግእዙ ልዩ ኹለተኛም ማለት ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ አግባብ ልዩ እንግዳ ከተለመደውና ባብዛኛው አስተዋይ/አመዛዛኝ/ምክንያታዊ ሰው ከሚቀበለው ወጣ ያለ በሚል ፍቺ ተጠቅሜበታለሁ፡፡

አንዳንዶች ፈሪሃ እግዚአብሔር ካለመኖር እና ጭርሱኑ ከሕሊና መለየት ይሁን ሆዳቸው አምላካቸው አድርገው ይሁንከዐቅም ማነስም ይሁንአከርካሪ አልባ ከመሆንም ይሁንእንደ ብአዴን ሞቶ የተወለደ (stillborn) በመሆን ይሁንየባላገር ፖለቲከኛበመሆን ይሁንየሥልጣን ጥማት ዐቅላቸው አሳጥቶት ይሁንወዘተ. ኢትዮጵያ አገራችንን በወሳኝ ሰዓት እየተነሡ የሚፈታተኗትካልእ ፍጥረታትአሉ፡፡ አለመታደል ሆኖ አገራችን የእነዚህ ካልእ ፍጥረታት ደሀ ሆና አታውቅም፡፡

እነዚህ የተጠቀሱት ጉዶች ለምን ይሆን ልቡሳነ ሥጋ አጋንንት መሆንን የመረጡት? ለምን ይሆን ሕይወቱን በሙሉ ከሰው በታች በግፍና በበደል ውስጥ ለኖረ ሕዝብ ጥፍጣፊ ርኅራኄና ሰብአዊነት ያጡት? በባዕድ አገር መሼጦ ሆነው ሲያበቁ አገር ቤት ያለ ሕዝባችንን ሰቆቃ የሚያራዝሙት? በኢትዮጵያዊነትበዐምሐራነትበክርስትና ስም እየነገዱበባዕድ አገር የሚኖረውን ወገን እያጭበረበሩ ርጥባን በመሰብሰብየአንጋሽነትአባዜ ተጠናውቶአቸው ሕይወታቸውን አስይዘው ለትግል የወጡትን በመከፋፈል የተጠመዱ? ርእሰ መጻሕፍቱ እነዚህንካልእፍጥረታት የአምልኮ መልክ ያላቸው ኃይሉን ግን የካዱት ብሎ ይገልጻቸዋል፡፡ እንዴት ዓይነት መረገም ቢሆን ነው ከወያኔ ሕወሓትከኦነግ (በግልባጩ ኦሕዴድ/‹ብልግና›) እንዲሁም ከነዚህ ፈጣሪ ሻእቢያ ጋር ብአዴናዊ አሽከር ሆነን ካልሠራን ሞተን እንገኛለን ያዙኝ ልቀቁኝ እያሉ የሚቱት?

አንዳንዴ እንደዚህ ዓይነትፍጡሮችመኖራቸውና ከእነርሱ ጋር አንድ ፕላኔት መጋራታችን ከፍተኛ መረገም ሆኖ ይሰማኛል፡፡ ምነው ኢትዮጵያ እንደነዚህ ዓይነቶቹ እሾኽ እና አሜኸላ በብዛት የበቀሉባት አገር ሆነች? ለምንድን ነው ምስጢሩ ያልገባቸው ግለሰቦችአገዛዛዊ ያልሆኑ መደበኛና ኢ-መደበኛ ብዙኃን መገናኛዎች  ከነዚህካልአን ፍጥረታት ጋርአንድ ጎራ እንደሆንን እና የሐሳብ ልዩነት ብቻ እንዳለን አድርገው ጉዳዩን የሚያቃልሉት? በእኔ እምነት ውገናቸው ከጠላት እንጂ ከተበደለውና ፍርድ ከተጓደለበት÷ ልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራ ሲቀበል ከኖረው እና አሁንም እየተቀበለ ከሚገኘው ሕዝብ ጎን አይደለም፡፡

አዎን! ከእንዲህ ዓይነቱ ምልልስና አተካሮ ርጉም ዐቢይና አገዛዙ እንደሚያተርፍ ጥርጥር የለውም፡፡ ይሁን እንጂ በመልከስከስና በመርመጥመጥ ከመጓዝ ደፍርሶ መጥራት የግድ ይላል፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ርጉም ዐቢይና አገዛዙ ተጠጋግኖሊቀጥል የሚችልበት ዕድል የለውም፡፡ የተፈጥሮ ሞቱን መሞቱ አይቀሬ ነው፡፡ ርጉም ዐቢይን ስናስወግድ ግን ሌላና ማይጠገን ጥፋት ፈጽመን መሆን የለበትም፡፡ የርጉም ዐቢይ አገዛዝ የመንፈስ አባቱ ወያኔ ሕወሓት ነው፡፡ ኦነግ በአሜባዊ ቅርፁ ደግሞ ራሱ ብልግናየተሰኘው ኦሕዴድ ነው፡፡ ሰሞኑን ኦነጋውያን አሜቦች (በብዙ ኢትዮጵያውያን ደም ተጠያቂ የሆነው ጀዋር እንዲሁም ፊደል የቆጠረ የማይመስለው ስንኩል አእምሮ ጸጋዬ አራርሳ ወዘተ.) አገዛዛችን ተናጋ ብለው ሲወራጩ እያስተዋልን አይደለም? ታዝባችሁ እንደሆነ ከአገዛዙም ወገን ይሁኑ በተቃዋሚም ስም እያጭበረበሩ ያሉ በሙሉ በዚህች ሰቆቃ በበዛባት ምድርና የስቃይ ጥግ እያየ ባለ ሕዝባችን የግፍ ዘመንን በዋናነት የሚያራዝሙት ነፃ በሆነ ባዕድ ምድር የሚገኙካልአንፍጥረታትመሆናቸው ሁሌም ይገርመኛል፡፡ ምን ዓይነት መረገም ቢሆን ነው ነፃ ምድር እየኖሩ በስሟ በሚነግዱባት አገራችን እና በስሙ በሚነግዱበት ሕዝባችን በተግባር ባርነት የሚመኙለት?

እውነት ውሎ አድሮ መገለጡ አይቀርምናየዐምሐራ ፋኖእውነቱን የሚጋፈጥበት ሰዓት ዘግይቷል ካልተባለ አሁን ነው፡፡ ‹እውነቱ ምንድን ነው?› የሚል ጲላጦስያዊ ጥያቄ የሚያነሡ እንዳሉ እሙን ነው፡፡ እውነቱ የዐምሐራ ፋኖ ይዞ የተነሣውን ዓላማና ግብ መሠረት ያደረገ ራእይ ያለው ድርጅት አሁንም የለውም፡፡ በነገራችን ላይአፋብንእንደ ብአዴን ሞቶ የተወለደ ነው፡፡እንግዴ ልጅነው፡፡ የዐምሐራ ፋኖን የሚወክልና የሚመጥንአካልአይደለም፡፡ እንግዴ ልጅነቱም ለወያኔ ለኦነግ ነው፡፡ የነሱም መጠቀሚያ ከሆነ በኋላ ተቆርጦ የሚጣል ነው፡፡ ከጊዜያዊ አመራሮቹ ጥቂቶቹ (ዘመነዐሥረስምሬ ወዳጆ) አንድም ብአዴናዊ መሠረት ያላቸው÷ ወዲህም በክህደት የታወቁ ፈጣሪያቸው ወያኔየሚናፍቃቸው› ‹የባላገርፖለቲከኞችናቸው፡፡ የዐምሐራ ፋኖ ተለይ የዐምሐራ ሕዝብ ባጠቃላይ እውነቱን መጋፈጥ አለብህ፡፡ በጎጥ በቀዬ በወንዝ መሸጎጡን አቁመህ የሕዝብህን ህልውና እና ትልቁን አገራዊ ሥዕል ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ በሽታውን የደበቀ መድኃኒት የለውም እንዲሉ ውስጥ ውስጡን የሚንተከተከተው ማልጎምጎም ይፋወጥቶ ኹነኛ መፍትሔ ያሻል፡፡

ካልአን ፍጥረታት ላልናቸው ዓይነተኛ ምሳሌዎች ካስፈለገን ያወቀ መስሎት እንደ ነሐስ የሚንሿሿ ለጥፋት ብቻ ሲሆን ብቅ የሚለው የፖለቲካዊ ስቶኮልም ሲንድረም ሰለባ የሆነው ልደቱ እና የዕድሜ ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰብጀምበሩእየጠለቀችበት ያለውበማንነት ቀውስ እና በብአዴናዊ ጭንጋፍነት የሚታወቀው አንዳርጋቸው አሉልን፡፡ በኢ-መደበኛ ሚዲያዎች የሚወራ ተከታዮችም አበጅተዋል፡፡ ሲያልቅ አያምር አሉ!!!

አንዳንዶች በክብር ጀምረው በኀሣር/በውርደት ያጠናቅቃሉ፡፡ ሊቃውንት አባቶች ሲናገሩ ያለፈ ጽድቅ አይጠቅምምየዛሬ ማንነት እንጂ፡፡ ደግሞ ደጋግሞ እንደ እሪያ መጨማለቅ ሰውነት አይደለም፡፡ እንደዚህ ዓይነቶቹ ተደጋጋሚ አጥፊዎች በመሆናቸው ሊቃውንት የማይፈወሱ ድውያን÷የማይመለሱ ጊጉያን (በዳዮች) ይሏቸዋል፡፡

ወገኔ! ኢትዮጵያዊ ከወገኑ ጋር ሕዝብ ለሕዝብ በሚደረግ ግንኙነት ረገድ ጊዜው ሲፈቅድ ለመነጋገር ችግር የለበት፡፡ እንደ ሕዝብምነፃ አውጪአንጠብቅ፡፡ ዐቅማችን የፈቀደውን የየራሳችንን ድርሻ እንወጣ፡፡ በስንፍና መና ከሰማይ እንዲወርድልን አንጠብቅ፡፡ ኢትዮጵያን የሚታደጋትነፃ አውጪድርጅት አይደለም፡፡ ከግማሽ ምእት ዓመት በላይ ለኢትዮጵያ ጠንቅ በሆኑነፃ አውጪተብዬ ድርጅቶች (ሻእቢያሕወሓት እና ኦነግበሕፅን ዘላለማዊው አሽከር ብአዴን ሳይረሳ) እንወቅባቸው፡፡

ጨለማ ከብርሃን ጋር ኅብረት እንደሌለው ሁሉ ከነዚህ አጋንንታዊ ድርጅቶች ልጣቸው ከራሰ ጉድጓዳቸው ከተማሰ አለቆቻቸው ጋር ኅብረት የለንም፡፡ ላገራችን ኢትዮጵያ እና ለሕዝቧ ዘላቂ ሰላም የምንሻ ከሆነ ከየትም ጪው ዶቄቱን አምጪው (the end justifies the means) ከሚል የስንፍናና ድንቊርና አካሔድ ባስቸኳይ ልንላቀቅ ያስፈልገናል፡፡ ሕገ ወጥ አቋራጭ መንገድ የትም አያደርስም፡፡ በድቡሽት ላይ ቤት አይገነባም፡፡ የወደፊቱን መልካም ሊጥ በብአዴናዊሻእቢያዊሕውሓታዊ እና ኦነጋዊ የገማ የሸተተ እርሾ ለማብኳት እና ለመጋገር አንሞክር፡፡ ውጤቱ ሳይታለም የተፈታ ነውና፡፡ የሚወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል እንዲሉ፡፡

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.