ሙሉጌታ በአገር ናፍቆት በጠና ታመመ፤ ሙሉጌታ በወገን ናፍቆት በጠና ታመመ፤ ሙሉጌታ ሉሌ በአሜሪካ ደህና ኑሮ እየኖረ ኢትዮጵያን መርሳት አቃተው፤ በአሜሪካ በነጻነት እየኖረ በጭቆናና በእስር ቤት የሚሰቃዩትን ወገኖቹን በአጠቃላይ፣ ጋዜጠኞችን በተለይ እያሰበ ይጨነቃል፤ በአሜሪካ ያገኘው ነጻነት በኢትዮጵያ ያጣውን ነጻነት ሊተካለት አልቻለም፤ ነፍሱ የተጠማችው የኢትዮጵያን ነጸነት ነው፤ የኢትዮጵያን ነጻነት እንደተጠማች እያለቀሰች ዐረገች፤ የኢትዮጵያ አምላክ ጩኸትዋን ይስማላት! የሌሎችንም ጩኸት ለአምላክ ታሰማ!
ሙሉጌታ ሉሌ......... [ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም]
ሙሉጌታ በአገር ናፍቆት በጠና ታመመ፤ ሙሉጌታ በወገን ናፍቆት በጠና ታመመ፤ ሙሉጌታ ሉሌ በአሜሪካ ደህና ኑሮ እየኖረ ኢትዮጵያን መርሳት አቃተው፤ በአሜሪካ በነጻነት እየኖረ በጭቆናና በእስር ቤት የሚሰቃዩትን ወገኖቹን በአጠቃላይ፣ ጋዜጠኞችን በተለይ እያሰበ ይጨነቃል፤ በአሜሪካ ያገኘው ነጻነት በኢትዮጵያ ያጣውን ነጻነት ሊተካለት አልቻለም፤ ነፍሱ የተጠማችው የኢትዮጵያን ነጸነት ነው፤ የኢትዮጵያን ነጻነት እንደተጠማች እያለቀሰች ዐረገች፤ የኢትዮጵያ አምላክ ጩኸትዋን ይስማላት! የሌሎችንም ጩኸት ለአምላክ ታሰማ!
Filed in: Amharic