>

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የቡና እና የጊዮርጊስን የደርቢ ጨዋታ ለመታደም አዲስ አበባ ስታድየም ቢገኝም ፌደራል ፖሊስ እንዳይገባ ከልክሎታል።

ስታዲየም የሄድነው ለምርጫ ቅስቀሳ አይደለም!!!” 

  እስክንድር ነጋ

•ተረኝነቱ እዚህ ተደርሷል!

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የቡና እና የጊዮርጊስን የደርቢ ጨዋታ ለመታደም አዲስ አበባ ስታድየም ቢገኝም ፌደራል ፖሊስ እንዳይገባ ከልክሎታል።
ዘጋቢ ዮናስ አበራ
—-
ዛሬ በተከናወነው የጊዮርጊስና የቡና ጨዋታ ላይ ለመገኘት ወደ ስታዲየም ያቀኑት የባልደረስ ስዎች እንዳይገቡ ተከልክለዋል በተባለው ጉዳይ ላይ እስክንድር ነጋን ከደቂቃዎች በፊት አነጋግሬው ነበር ።እስክንድር በወከባና በማስገደድ እስታዲየም እንዳይገቡ መደረጉን ገለፆልኛል::
 ወደ ስፖርት እና ከፖለቲካ የፀዳ ወደሚባለው ቦታ ማቅናቱን ለምን ፈለጋችሁት?  ለሚለው ጥያቄዬ እስክንድር ሲመልስ ” እኛ እዚያ የተገኘነው የጊዮርጊስና የቡና ደጋፊዎች ከግጭትና ከመራራቅ ወጥተው ወደ እንድነት መንፈስ እንዲገቡ መልእክት ለማስተላለፍ ነበር:: የቡናና የጊዮርጊስ ደጋፊዎች አንድነት ለአዲሰአበቤዊያን አንድነት አስተዋፆ አለው” ብሏል::  ከዚህ የዘለለ ሌላ የፖለቲካ አጀንዳ በእርግጥ አልነበራችሁም ወይ?” ስልም ጠይቄው ነበር:: ሲመልስም ” አልነበረንም:: እኛ ወደዚያ የሄድነው ለምርጫ ቅስቀሳ አይደለም” በማለት መልሶልኛል::
Filed in: Amharic