“ ስታዲየም የሄድነው ለምርጫ ቅስቀሳ አይደለም!!!”
እስክንድር ነጋ
•ተረኝነቱ እዚህ ተደርሷል!
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የቡና እና የጊዮርጊስን የደርቢ ጨዋታ ለመታደም አዲስ አበባ ስታድየም ቢገኝም ፌደራል ፖሊስ እንዳይገባ ከልክሎታል።
ዘጋቢ ዮናስ አበራ
—-
ዛሬ በተከናወነው የጊዮርጊስና የቡና ጨዋታ ላይ ለመገኘት ወደ ስታዲየም ያቀኑት የባልደረስ ስዎች እንዳይገቡ ተከልክለዋል በተባለው ጉዳይ ላይ እስክንድር ነጋን ከደቂቃዎች በፊት አነጋግሬው ነበር ።እስክንድር በወከባና በማስገደድ እስታዲየም እንዳይገቡ መደረጉን ገለፆልኛል::
ወደ ስፖርት እና ከፖለቲካ የፀዳ ወደሚባለው ቦታ ማቅናቱን ለምን ፈለጋችሁት? ለሚለው ጥያቄዬ እስክንድር ሲመልስ ” እኛ እዚያ የተገኘነው የጊዮርጊስና የቡና ደጋፊዎች ከግጭትና ከመራራቅ ወጥተው ወደ እንድነት መንፈስ እንዲገቡ መልእክት ለማስተላለፍ ነበር:: የቡናና የጊዮርጊስ ደጋፊዎች አንድነት ለአዲሰአበቤዊያን አንድነት አስተዋፆ አለው” ብሏል:: ከዚህ የዘለለ ሌላ የፖለቲካ አጀንዳ በእርግጥ አልነበራችሁም ወይ?” ስልም ጠይቄው ነበር:: ሲመልስም ” አልነበረንም:: እኛ ወደዚያ የሄድነው ለምርጫ ቅስቀሳ አይደለም” በማለት መልሶልኛል::