‹‹የሃይማኖት ጉባኤ›› የሚባል የአገዛዙ ተቀጥላመሣሪያ እንጂ የሃይማኖት ተቋም አናውቅም!

ከይኄይስ እውነቱ

 

ኢትዮጵያን ከሚያፈርስ እና ሕዝቧን ቁም ስቅል ከሚያሳይ አገዛዝ ጋር እጅና ጓንት ሆኖ የሚሠራ ለዚሁ አፍራሽ ዓላማ የተቋቋመ ድርጅት‹‹ኢትዮጵያ›› የሚል ክቡር ቅፅል ሊሰጠውም አይገባም፡፡ ከመነሻውም የተለያየሃይማኖትበእምነት ጉዳይ የአንድነት ጉባኤ ሊኖረው አይችልም፡፡ ጨለማ ከብርሃን ጋር ኅብረት ሊኖረው አይችልምና፡፡ ክርስቶሰ ከቤልሆር ጋር መስማማት እንደሌለው ሁሉ፡፡ ስለዚህ ተቋም ከዚህ ቀደም ብዙ ተብሏል፡፡ አካፋን አካፋ ማለት ተገቢ ነው፡፡ እንኳንይሄ ‹‹ጸጕረ ልውጥ›› ተቋም ይቅርና የጥንቶቹም የእምነት ተቋማትበአገዛዙ ቊጥጥር ሥር ከዋሉና ዓላማቸውን ከሳቱ ዘመናትተቆጥረዋል፡፡ ቢያንስ በማውቀው በኢኦተቤክ አብዛኛውአገልጋዮቹየዓላውያን አገዛዞች ሎሌዎች ሲሆኑእንደ ዴማስ ሆዴ ይሙላ ደረቴይቅላ ብለው÷ ደንደስ አበጅተው በሥጋዊ ምቾት የሚቀማጠሉየክርስቶስን መንጋ በትነው ለ‹አውሬአሳልፈው የሰጡሰማይ ሩቅአደራ ጥብቅ ተብለው ከእረኞች አለቃ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ቊርጥም አድርገው የበሉ የአምልኮ መልክ እንጂ መንፈሳዊነት የሚባልየሌለባቸው በቀሚስና ካባ ውስጥ የተደበቁ ምእመኑን ለማይነጥፍገንዘቡ ብቻ የሚፈልጉጸሐፍት ፈሪሳውያንመሆናቸው የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡

በመሆኑም ይህ ‹‹የሃይማኖት ጉባኤ›› የተባለው ድርጅት የውሸትየፖለቲካ ማኅበር አቋቁሞ ለፈረንጆቹ ፍጆታ ለላንቲካ ለሚደረገው‹‹ምርጫ›› የርጉም ዐቢይ አጃቢ ሆኖ ቢሳተፍ ይሻለው ነበር፡፡ እንዲህማፈሪያ የሆኑ ግለሰቦችና ተቋማት እንደ አሸን የፈሉበት ዘመን ላይመድረሳችን በራሱ መረገም ነው፡፡ ይሄ ድርጅት በምን የሞራል ልዕልናነው አገራዊ ምሕ የሚጠራው? እነማንን ነው የሚጠራው? ኧረእባካችሁ ይሄ ፌዝ ይቁም! የኢኦተቤክ ምእመናን! ከዚህ ቀደም አገዛዙበተቆጣጠረው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቀርበው ከሥርዓት የወጣግርግር አታስታውሱም? እነርሱ ከፈለጉ አገዛዙ አገርን ማፍረሱንደሀመበደሉንና ፍርድ ማጉደሉን ቀጥልበት ብለው ይለምኑለት፡፡ እኛየተዋሕዶ ልጆች ግን የዚህ የቤልሆር ጉባኤ እድምተኞች መሆንየለብንም፡፡

በመጨረሻም ቊጥራችን ቀላል የማይበል የኢኦተቤክ ምእመናንእስከ መቼ የበዓል ክርስቲያን ሆነን እንዘልቃለን? እስከ መቼ ለዓላውያን ያደሩ ሐሰተኛአገልጋዮችተገዢ ሆነን ራሳችንን እናታልላለን? በዚህበከፋ ኑሮ እስከ መቼ ለፍተን ያገኘንውን ገንዘብ ለካድሬዎችና ለሌቦችእያስረከብን ‹‹እልል እያልን እና እያጨበጨብን›› እንቀጥላለን? አንዳንዱም በዘረፈው ገንዘብ የኀጢአት ስርየት የሚያገኝ እየመሰለውራሱን እስከ መቼ ያታልላል? ለቤተክርስቲያን እያላችሁ የምትሰጡትገንዘብና ማናቸውም ሥጦታ የጣዖት አምላኪዎች ለሆኑትእውነተኛ አገልጋዮችን÷ መነኮሳትን÷ የአብነት መምህራንንና (ሊቃውንትን) ተማሪዎች እና ምእመናን በጠራራ ፀሐይ በግፍ ላስገደሉአድባራትንና ገዳማትን እስከነ ቅርሶቻቻ ላወደሙ ለርጉም ዐቢይናታማኝ ተላላኪው አዳነች አበቤና ግብር አበሮቻቸው ኪስ እንደሚገባ ታውቃላችሁ? የኢትዮጵያ ምእናን ለመሆኑ እንዳታስተውሉ ማን አዚምአደረገባችሁ? የኢኦተቤክ በቅጥረኝነትና በካድሬነት ያሰማራቸውሐሳውያንአገልጋዮችታላቁ የድኅነት ቀን ስቅለተ ክርስቶስን እንኳንመታገሥ አቅቷቸው ጥቂት የማይባሉ አድባራትና ገዳማት በዓመትአንዴ የሚፈጸመው የግብረ ሕማሙ ልዩ የጸሎት ሥርዓት ተቋርጦለ‹ገንዘብ ዝርፊያየሚውል የቴሌቶን ቀን ካደረጉት ከራርሟል፡፡በእጅጉ ያሳዝናልያማልም፡፡ በራሳችን ሥርዓትና እውነተኛ አባቶችመሪነት ያላደረግነውን ጸሎተ ምሕ ርጉም ዐቢይ ባሰማራቸው ሎሌዎች አማካይነት ማድረግ የምንችል ይመስላችኋል? እንደባለአእምሮ እንመላለስ፡፡

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.