>
5:13 pm - Monday April 19, 2838

"ተቃዋሚ ስትሆን የዝሆን ቆዳ መልበስ ያስፈልግሀል!!!"  (ፕ/ ር ብርሃኑ ነጋ) 

   ምክንያት እነ ፀጉር ሰንጣቂዎች  ደረጃ መዳቢዎች ኩሩ ፓለቲከኞች አንድነትን እንዴት ማምጣትና አንድነትን  እንዴት ማስጠበቅ  ሳይረዱ   ራሳቸውም  አንድ ሳይሆኑ አንድነት አሁንም አንድነት  የሚሉ የነሱን ትችት ፍረጃ ስድብ ሁሉ መቋቋም የሚያስችል ጥንካሬ ይጠይቃል ።
  በበኩሌ  በኔይቱ እንቱፍንቱ  እንኳ ወደኔ የሚሰነዘሩት የራሴ ወገን የምላቸው እኔን የሚጎዱ ።
ኤች !! ከእንግዲህ  እርም ይሁንብኝ ብዬ  እንድተወው  የሚያደርጉ ሀሞት የሚያፈሱ ትችቶች ይደርሱኛል ።
  አንድነት ሳይኖረን ስለአንድነት መዘመሩ  ብዙ መቶ ዓመታትን ብንቆጥርም ለውጥ አይመጣም  ባልተሄደበት መንገድ ድክመትን ገምግሞ ካልተሄዴ  የኔ ብቻ ለሀሳር  የውኃ ቅዳ የውኃ መልስ  ፖለቲካ የአንድነት ወሬያችን 50 ዓመት አስቆጠረ ።
ለኔ ማንኛውም በዚህ ዘረኛና ሴረኛ ሀገር አፍራሽ በሆነው በሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ ( ሕውሓት) ላይ ጠጠር የወረወረው ሁሉ ወዳጄ ነው ዝም ብለው ሁሉም በኛ ይመራ የሚሉ በውጩ ዓለም የሚኖሩ የተቃዋሚ ተቃዋሚ ለሆኑት ይች ፅሁፌ ለነሱ ናት ፣  መታሰቢያም ትሁንልኝ ።
ፀረ ሕውሓት ሁኖ ከመጣ  !!!!!
* ወራሪው ፋሽሽቱ  መሶሎኒ ቢመጣ እደግፈዋለሁ ።
ለኢትዮጵያ ከሕውሓት የበለጠ አደገኛ  ጠላት ገጥሟት አያውቅምና ።
በቅኝ የተገዙ  የአፍሪካ ሀገራት ቅኝ ገዥዎቻቸው ቋሚ ወሰናቸው  አስከብረውላቸው ነው የወጡትና ። የደቡብ አፍሪካው የነጭ ዘረኛው አፓርታይድ እንኳ ጥቁሮችን ቢገድልም ግፍ ቢፈፅምም ሀገሪቱን አልገደለም እነሆ ዛሬ ላይ ያች በነጭ ዘረኞች ተይዛ የነበረች ሀገር ለኛም መጠለያ ሁናለች በአፍሪካ ከአውሮፓውያን እኩል ደረጃ ያላት ታላቅ ሀገርን መስርተዋል ።
ሕውሓት መልከ ጥቁር ከመሆኑ በስተቀር በዘረኝነቱ እኩል ከአፓርታይድ አንድ ነው የሚለየው ግን የሚገዛትን ሀገር ቀስ በቀስ እንደጨው እያሟሟ እያሟሟ ያለበት ሁኔታ ነው የኢትዮጵያ ጠረፎች በሙሉ ወደጎረቤት ሀገራት እያጠጋጋ ነው  መሀከል ኢትዮጵያንም የዘር ኬላ የቋንቋ አጥር እየገነባ ነው
#ቦንብ እየቀበረ ነው ።
ሕውሓት እንደዛ አይደለም ፣
ቀስ በቀስ የኢትዮጵያን ጠረፎች ቀስ በቀስ ወደጎረቤት ሀገራት እያጠጋጋ ይገኛል ።
በደንበር የሚገኙት ኢትዮጵያውያንን ከኢትዮጵያ ይልቅ ወደጎረቤት ሀገራት ግንኙነት እንዲፈጥሩ አንዳንዴማ ኢትዮጵያውያን ከነመሬታቸው ለጎረቤት ሀገራት እያስረከባቸው እናያለን ።
ይህን  በሚቃወሙት ላይ በሕውሓት የአግአዚ ሰራዊት እስከ ዘር ማጥፋት ሲካሄድባቸው እናያለን ።
ሕውሓት ሀገር በቀል ፀረ ኢትዮጵያ ወራሪ ኃይል ነው ።

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=10206422756028778&id=1264962997

Filed in: Amharic