>

የኢ/ር ስመኘው ገዳዮች ጄ/ል ክንፈ እና ዶ/ር ደብረፂዮን ናቸው!! (ስዩም ተሾመ)

የኢ/ር ስመኘው ገዳዮች ጄ/ል ክንፈ እና ዶ/ር ደብረፂዮን ናቸው!!
ስዩም ተሾመ
የኢንጂነር ስመኘውን አሟሟት አስመልክቶ ፖሊስ ያቀረበውን የምርመራ ውጤት እንዳለ እንቀበለው። እሺ…እንጂነር ስመኘው ራሱን አጥፋ። ይህ ሰው ራሱን ያጠፋበት ምክንያት ምንድነው? የሀገሪቱን ትልቅ የግንባታ ፕሮጀክት በኃላፊነት ሲመራ የነበረ ሰው ነው። መስቀል አደባባይ ላይ ራሱን ከማጥፋቱ በፊት ፍላሚንጎ ወደሚገኘው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ቢሮ እየሄደ ነበር። የሚሄደው ስለ ህዳሴው ግድብ ግንባታ አጠቃላይ ሂደት መግለጫ ለመስጠት ነው።
ከዚያ ቀደም ብሎ ጠ/ሚ አብይ አህመድ የህዳሴው ግድብ ግንባታ አሁን ባለው አካሄድ በአስር አመት ውስጥ እንደማይጠናቀቅ መናገራቸው ይታወሳል። ኢ/ር ስመኘው ግን “የግድቡ ግንባታ ከ60% በላይ ደርሷል” እያለ መግለጫ ሲሰጥ ኖሯል። ይህ ሰው እንዲህ ያለ የውሸት መግለጫ ሲሰጥ የኖረበት ምክንያት አስመልክቶ ከዚህ ቀደም ከዶ/ር ደብረፂዮን ገ/ሚካኤል ጋር ያደረገውን የኢሜል ልውውጥ እንደ ማሳያ መጥቀስ ይቻለል። እነ ዶ/ር ደብረፂዮን እና ጄ/ል ክንፈ ለህዳሴው ከተመደበው በጀት ውስጥ ወደ 70 ቢሊዮን የሚሆነውን ሙጥጥ አድረገው ሲዘርፉ ኖረዋል። በተለይ ለሜቴክ የተሰጠው ስራ ግን ገና 30% ላይ ነው። 30% የሚሆነውን ሥራ ሳይሰሩ 90% የሚሆነውን በጀት የበሉት የሜቴክ እና ህወሓት ባለስልጣናት ኢ/ር ስመኘውን እያስገደዱ “የህዳሴው ግድብ ግንባታ ከ60% በላይ ደርሷል” እያለ እንዲናዘዝ ሲያደርጉት ኖረዋል።
በድንገት ዶ/ር አብይ መጣና በህዳሴው ግድብ ጉብኝት ያደርጋል። በቦታው ያለውን የውሸትና የሌብነት ክምር ከተመለከተ በኋላ “ይህ ውሸትና ሌብነት ማብቃት አለበት። የኢትዮጵያ ህዝብ እውነታውን ማወቅ አለበት። የህዳሴው ግድብ ገና 30% ላይ ሲሆን 90%ቱ በጀት ተዘርፎ አልቋል ብለህ እቅጩን ተናገር” የሚል መመሪያ ይሰጡታል። ከጉብኝቱ መልስ ጠ/ሚ አብይ አህመድ ከምሁራን ጋር ባደረጉት ስብሰባ “የህዳሴው ግድብ አሁን ባለው አካሄድ በ10 አመት ውስጥ እንኳን አይጠናቀቅም” ብለው ተናገሩ።
የሀገር ውስጥና የውጪ ሚዲያዎች ወደ ኢ/ር ስመኘው ስልክ በመደወል “ይሄ ነገር እንዴት ነው?” ብለው ጠየቋቸው። ሰውዬው በከፍተኛ ግራ መጋባት ውስጥ ሆነው “ቆይ ከመንግስት ኮሚኒኬሽን ጋራ ተናጋግሬ ምላሽ እሰጣለሁ” ማለት ጀመሩ። በቀጣይ ቀናት ወደ አዲስ አበባ መጡ። ዋና ዋና የመንግስት ሚዲያዎችን ጠርተው ፍላሚንጎ ወደሚገኘው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ፅ/ቤት በመሄድ ላይ ሳሉ መስቀል አደባባይ ራሳቸውን አጠፉ።
ኢ/ር ስመኘው የሚሰጡት መግለጫ ምን የሚል ነበር? “የግንባታ ሥራው ገና 30% ላይ እያለ 90% በጀት መዘረፉን ደብቄ ሥራው ከ60% በላይ ደርሷል እያልኩ የሌቦችን ስራና ዘረፋ ስደብቅ፣ ሀገርና ህዝብን ስዋሽ…ስዋሽና ስዋሽ ኖሬያለሁ” የሚል ነው። ይሄ “Professional Suicide” ይባላል!!! ኢ/ር ስመኘው ላለፉት 6 አመታት ሙያዊ ኃላፊነቱን መወጣት የተሳነው፣ ሀገርና ሕዝብ ሲያዘርፍ የኖረ ሙያዊ ክብርና ስነ-ምግባሩ የተገፈፈ “ተራ” የዘራፊዎች መጨዋቻ እንደነበር በራሱ ላይ ከሚመሰክር ራሱን ቢያጠፋ ይመርጣል። በዚህ መሰረት ኢ/ር ስመኘው ራሱን አጠፋ!!!
ኢንጅነሩ ራሱን ሲያጠፋ ከሁሉም ቀድመው የአዞ እምባ ማንባት የጀመሩት ገዳዮቹ ናቸው። የኢ/ር ስመኘው ገዳይ ሽጉጥ አይደለም። ራሱ ግለሰቡም አይደለም። ከዚያ ይልቅ እጁን የኋሊት ጠፍሮ በጉልበት እያስፈራራ ሲያስዋሸዋ የኖረው ጄነራል ክንፈ፣ ለሙያው እንዳይገዛ ከላዩ ላይ የዕብሪት ትዕዛዝ ሲያዘንብበት የነበረው ዶ/ር ደብረፂዮን ናቸው። በዚህ መልኩ ህሊናዉን ሸጦ፣ ውሸት እየተናገረ፣ የእነሱን ዘረፋ እየደበቀ እንዲኖር ያደረጉት፣ ሙያዊ ክብርና ዝናውን የገፈፉት፣ በመጨረሻም ራሱን እንዲያጠፋ ያደረጉት ጄ/ል ክንፈ እና ዶ/ር ደብረፂዮን ናቸው።
Filed in: Amharic