ከድር እንድሪስ
ከዳዑድ ኢብሳ ኦነግ ጋር ከዓመታት በፊት በአስመራ የተለያዩት ብርጋዴር ጀነራል_ከማል_ገልቹ ቲም ለማን ተቀላቀሉ:: የኦሮሚያ አንድነትና ነፃነት ግንባር መሪ ብርጋዴር ጀነራል ከማል ከዳኡድ ኢብሳ ኦነግ ጋር ከተለያዩ በኋላ ከኤርትራ ወጥተው በኡጋንዳ እንደቆዩ ይነገራል:: “የትጥቅ ትግል ሲያደርጉ የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶች የትጥቅ ትግል ፋሽን ያለፈበት በመሆኑ ሰላማዊ ትግል ለማድረግ ወደ ሀገር ግቡ” በሚል የቀረበውን የዶ/ር ዓብይ ጥሪ ተቀብለው ወደ ኢትዮጵያ ገብተው የነበሩት ጀነራል ከማል:-
* ቲም ለማን በመቀላቀል
* የኦሮሚያ ፀጥታና ደህንነት ቢሮ ሀላፊ ሆነው ሹመት አግኝተዋል::
በብርጋዴር ጀነራል ከማል ገልቹ የሚመራው የኦሮሚያ አንድነትና ነፃነት ግንባር ወደ ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ ኦዴፓን ይቀላቀላል ተብሎ በሰፊው ሲነገር የነበረ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ድርጅቱ ዶ/ር ዓብይና ለማ መገርሳ ከሚመሩት ኦዴፓ ጋር ይቀላቀል-አይቀላቀል አልታወቀም፡፡ ነገር ግን ጀነራል ከማል ቲም ለማን ተቀላቅለው ይህን ትልቅ ሹመት አግኝተዋል:: ለጀነራል ከማል ገልቹ የተሰጠው ሹመት በተለይም የዳኡድ ኢብሳን ኦነግ እንደማያስደስት የቅርብ ሰዎች ይናገራሉ::