>

አማራን የማሽመድመዱ ዕኩይ ተግባር ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው (አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ)

አማራን የማሽመድመዱ ዕኩይ ተግባር ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው

 

አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ)

 

ብሶት የወለደው ጀግናው የኦነግ ሠራዊት ወያኔ/ኢሕወደግ ሲጠቀምበት የነበረውን የምኒልክ ቤተ መንግሥት ለሕዝብ ጥቅም ተቆጣጥሮ ሲያበቃ በግንቦት ሰባት/ኢዜማ አማካሪነት አማራን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ጠንክሮ እየሠራ መሆኑን ለመገንዘብ እንደተቻለ ሰሞነኛ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ቁልጭ ባለ ሁኔታ እያሳዩ ናቸው፡፡ ግንቦት 20/83 እንዴት አሁን ትዝ አለኝ በል?

ለብልኅ አይነግሩም ለአንበሣ አይመትሩም፡፡ በአቢይ አህመድ የሚመራው የድውያን ፖለቲከኞች አማራን እጉያው ድረስ ገብቶ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ዕኩይ ተግባር በተለይ ካለፈው ዓመት የሰኔ 15 ጭፍጨፋ ወዲህ ያለ አንዳች ሀፍረት በገሃድ እየታዬ ነው፡፡

ለአማራ ሕዝብ ኅልውና የሚቆረቆሩ ድርጅቶችና ግለሰቦች በየትኛውም ተቋም ይታቀፉ ቅንጥ ቅንጣቸውን እየተመቱ አንድም በነፍስ አንድም በአካል ከትግል ሜዳው እንዲርቁ እየተደረጉ ነው፡፡ ንቁ ንቁ የአማራ ሕዝብ አለኝታዎች በዚህ መልክ ከሜዳው ገለል ሲሉ አማራን ከወያኔው ዘመን በከፋ በምን መልክ ሊያጠፉት እንደሚችሉ ከወዲሁ መገመት አይከብድም፡፡ ከብቶችን ለመዝረፍ በቅድሚያ እረኞችን ማጥፋት ተገቢ መሆኑ ለማንም የተሠወረ አይደለም፡፡ ስለሆነም በብአዴንም ውስጥ ቢሆን ለአማራው ደግ የሚያስቡና የሚቆረቆሩ ካሉ አማራን ለማጥፋት በቅድሚያ እነዚያን ማጥፋት ለነገ የሚያሣድሩት አይደለም፡፡ ለዚህም ተግባር ቆሞ ቀር አእሩግ ፖለቲከኞች ለአማካሪነት አሰፍስፈዋል፡፡ 

አማራ አለመሆናቸው ከጉዳይ የማይጣፍ ሆኖ – ለምን ቢባል ሰውን ለመውደድ ሰው መሆን ብቻውን በቂ በመሆኑ – የግንቦት ሰባት ሰዎችና ኢዜማ በሚባለው የነዚሁ ሰዎች ጥፍጥፍ ድርጅት ውስጥ ያሉ አማራ ጠል ግለሰቦች እያከናወኑት ያለው ድብቅ ሤራ ሳይጠቀስ አይታለፍም፡፡ ሁሉም ሒሣብ ማወራረዱ የማይቀር ቢሆንም አሁን ነገረ ሥራችንን ትክ ብለው ካዩት ብዙ የሚያንገበግብ ጉዳይ አለ፡፡ ሁል ጊዜም አንድ የሚጽናናኝ ነገር ደግሞ አለ – እሱም ሁሉም ነገር ባለበት አለመኖሩ፡፡

ያቺን “ፍኖተ ካርታውን ለአቢይ የሰጠነው እኛ ነን” የምትለዋን የአንዳርጋው ጽጌን ቀዳሚ ቃል ይዘን ከዚያ በፊትና በኋላ የተደረጉና እየተደረጉ ያሉ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን ስንመለከት ሁሉም ነገር እየተቀጣጨ የሚገኘውና የሁሉም ባለድርሻ አካላት አቢይ ተግባር የሆነው አማራን ሸኮና ሸኮናውን እየቀጠቀጡ ማሽመድመድ ነው፡፡ ይህ ዘመቻ የሚካሄደው በአፋቸው ኢትዮጵያውያን ነን በሚሉ ሰዎች ይሁን እንጂ መነሻው የዓለም አቀፍ ኢሉሚናቲዎች ፀረ-አማራና ፀረ-ኦርቶዶክስ በድምሩም ፀረ-ኢትዮጵያ ነባር ዘመቻ ቅጣይ መሆኑን ለመረዳት ቂጥኛም ከውርዴ የሚሞዳሞድበትን የወቅቱን ሀገራዊ የፖለቲካ ዐውድ ማጤን ብቻ በቂ ነው – ባጭሩ የሕወሓት አማራንና ኦርቶዶክስን የማጥፋት የለካቲት 68 ማኒፌስቶ ግዘፍ በነሳ መልክ እየተተገበረ ነው፤ከዚያም ባለፈ ሴቴኒዝም እንዲስፋፋ በስፋት ጥረት እየተደረገ ነው – ለማየት ያብቃችሁ በቅርቡ ሴትና ሴት፣ ወንድና ወንድ ሲጋቡ ጠ/ሚኒስትሩ ለክብር እንግድነት ይታደማል …፡፡ እነዚህ ጊዜ ሰጠን ብለው ከላይ እስከታች እንደቀትር እባብ የሚቅነዘነዙ የፖለቲካ ሴተኛ አዳሪዎች (ይቅርታ – ቃሉ ትንሽ ስለሚያስጠይፍ “ሸርሙጦች” ላለማለት ነው) አማራን ለማጥፋት ከዚህ ጊዜ በላይ ምቹ አጋጣሚ እንደሌለ አምነው በሙሉ አቅማቸው እየተራወጡ ይገኛሉ፡፡ እውነታቸውን ነው – ጌቶቻቸው አንድ ፈሊጥ አላቸው:- Hit the iron when it is hot! የሚል፡፡ በርግጥም ከወርቃማው ኢትዮጵያዊ ዘመን በፊት ታሪክ በአዳፋ እጆቹ አስተናግዶ መቀመቅ የሚከታቸው የመጨረሻዎቹ እንክርዳዶች ናቸው፡፡ ይህን ጠብቁ!!

እነአምባቸውንና አሣምነውን በይቺ ባቄላ ካደረች … ተረት በጊዜ አጠፉ፡፡ በሰበቡም የሚያስሩትንና ከፖለቲካ ጨዋታ ውጭ ማድረግ የሚፈልጉትን ሁሉ ባቀዱት መሠረት አደረጉ፡፡ በምትካቸውም የግንቦት ሰባት ሰዎችን በአማራው ላይ መደቡ፡፡ ለዚህና ለመሰል ተግባሮቻቸው ግንቦቶች ከጀርባ ሆነው እሥር ቤት የነበሩ ጅላጅል አማሮችን ከፊት በማሰለፍ አማራውን ለማነሁለል ሞከሩ – እምብዝም ባይሳካም፡፡ አማራ – በነገራችን ላይ አውቆ የተታለለ ይመስላል እንጂ – በቀላሉ አይታለልም፡፡ እንዲያውም የተታለለ እየመሰለ አጋጣሚውን ሲያገኝ ጉድ የሚሠራ ነው – አማራ፡፡ ምንም ያልተማረውን ባላገር አማራ ሂድና ለማታለል ሞክር – እየሣቀ አንተኑ ያነሆልልሃል፡፡ 

የአማራ ጠላቶች አሁን ከዳዴ አልፈው ቆመው እየሄዱ ያሉ ይመስላሉ፡፡ ሰሞኑን ደግሞ ትንታጎቹን እነዮሐንስ ቧ ያለውንና ተፈራ ወንድማገኝን ገለል አደረጉ፡፡ ሁለቱም ጎበዝ ነበሩ፡፡ አማራው በተስፋ የሚጠብቃቸው ነበሩ፡፡ ግን የአቢይ ሠይፍ በነፍስ ባይሆንም በአካል ከድርጅታቸው – ከእጅ አይሻል ዶማ አሽከር ድርጅታቸው – ገለል እንዲሉ አደረጋቸው፡፡ በነፍስ አይምጡባቸው እንጂ ይህስ ቀላል ነው፡፡ ይሄ አቢይ የሚሉት ጉድ ግን በዚህ ዕድሜው ይህን ሁሉ ፖለቲካዊ ሤራና ሸፍጥ፣ አፍዝ አደንግዛዊ የማጭበርበርና ሰውን በ“ፍቅሩ” የማነሁለል አጋንንታዊ ድግምትና መተት ከየት አገኘው? ያቺን የዐፄ ኃ/ሥላሤን ጦሰኛ የጣት ቀለበት አቀብለውት ይሆን? መጠርጠር ነው!

በተለይ ተፈራ ወንድምአገኝ ብርቱ ሰው ነበር፡፡ ለአማራውም ሆነ ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ እንደነበር ከሚያደርጋቸው ንግግሮች መረዳት ይቻል ነበር፡፡ ነገር ግን ጥሩ ዜጋ ሆኖ መገኘት ለአቢይ የቆረጣ ውጊያ ይዳርጋልና ሌሎችም ተጨምረው ተንሳፈፉ፡፡ አቢይ የክፋቱ ክፋት ዮሐንስን በሕይወት መኖር አለመኖሩ እንኳን የማይታወቀውን የመለስ ፋውንዴሽን የሚባል ሙትቻ ተቋም የበላይ ጠባቂ አድርጎ “መሾሙ” ነው፡፡ ይህ “ሹመት” ሰውዬውን በሞራልም ለመግደል የታሰበ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ በትግርኛ “ውፃዕ አይትበሎ ከምጽወፅዕ ግበሮ” ይባላል – በአማርኛ ስለመኖሩ አላውቅም፡፡ “ውጣ አትበለው እንዲወጣ ግን አድርገው” እንደማለት ነው፡፡ በነሱ ቤት ብልጥ ሆነው ሞተዋል፡፡

ኢዜማም በሉት ግንቦት ሰባት አቢይም በሉት ጃዋር እንደሚመጡ እናውቅ ነበር – በስማቸውና በያዙት መልክና ቁመት ሳይሆን በዕኩይ ምግባራቸው ፡፡ እንደሚያልፉም እናውቅ ነበር፡፡ማለፊያቸው ቀጭን መንገድም ልትመጣ በግንባር እየገሰገሰች ናት፡፡ ኢትዮጵያውያን ጸንታችሁ ቁሙ፡፡ ይህ ግብስብስ ዘመን ወደ ታሪክ ማኅደርነት ሊጠቀለል የቀረው እጅግ ጥቂት ጊዜ ነውና ከስህተት ተጠብቃችሁ ወደ ላይ አንጋጡ፡፡ ወጣቶችና ጎልማሦች ጊዜው የሚያዛችሁን የጀግንነት ተግባር ለመፈጸም የጊዜን ትዕዛዝ በተጠንቀቅ ጠብቁ – ጊዜና ፈጣሪ ጀግኖችን በጊዜው ይወልዳሉና በምታዩት ጽልመት አትደናገጡ፤ ሊሆን ግድ ነውና፡፡ ይህችን አገር ለመጉዳት የተሰባሰበ የጥፋት ሠራዊት ሁሉ የዶግ ዐመድ የሚሆንበት ዘመን እጅግ የተቃረበ በመሆኑ ደስ ይበላችሁ፤ የሚባለው ሁሉ ሳይሆን ያልቀረ በመሆኑ የምንለው ሁሉ እውነት ነው፡፡ ችግሩ ሞት ሲዘገይ የቀረ መምሰሉ ነው፡፡

እነቁጭ በሉዎችም ለጊዜው ተደሰቱ፡፡ በአማራው ላይ እንደልባችሁ ናኙበት፡፡ ቦርቁበት፡፡ ቋቱ እስኪሞላ እንደፈለጋችሁ አሽቃንጡበት፡፡ ቋቱ ሲሞላ ግን ወዮ ለእናንተ! በፋሲካ የተቀጠረች ገረድ ሁሌ ፋሲካ ይመስላታል፡፡ በትዕቢትና በዕብሪት የተወጠረ አካልም ሁሌ በአሸናፊነት ስሜት እንደታወረ ነው፡፡ጋዳፊም እኮ ከተደበቀበት የቆሻሻ ቱቦ ወጥቶ ሣንጃ በእንትኑ እስኪወደወድበት ድረስ የሊቢያ መሪ እንደሆነ ይሰማውና ያምንም ነበር፡፡ አምባገነኖች እንደዚህና እስከዚህም ገገማዎች ናቸው፡፡ ነገ የሚሞት አምባገነን ዛሬ ሚሊዮኖችን ሲጨፈጭፍና ሲያስጨፈጭፍ በውስጡ የመሸገው ዕብሪትና ትዕቢት አይፈቅድለትምና አንድም ርኅራሔ የለውም፤ ይህ ዓይነቱ ተፈጥሮም ያሣዝናል፡፡

Filed in: Amharic