>

"… ያለው የገዳ መስፋፋት፣ አስምሌሽን እና ወረራ እንጂ ተረኝነት አይደለም...!!!" ሥርጉተ ሥላሴ

“… ያለው የገዳ መስፋፋት፣ አስምሌሽን እና ወረራ እንጂ ተረኝነት አይደለም…!!!”
ሥርጉተ ሥላሴ

“ተረኝነት ስትል የባጀህ የእጭ ፖለቲካ አራማጅ ሁሉ ዕወቀው ጉድህን – “የብልፅግና መንግስት 11ኛ &12ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ እንዳይሰጥ ከልክሏል። አማራና እና አማርኛ ቋንቋን ማዳከሙ እንደቀጠለ ነው። ተረኝነት እንጂ ለውጥ የለም””
… ያለው የገዳ መስፋፋት፣ አስምሌሽን እና ወረራ እንጂ ተረኝነት በፍፁም አይደለም። ከዬኔታ ጎዳና ያዕቆብ በስተቀር ይህን እውነት የደፈረው የለም።
እሳቸው ከተረኝነት በላይ ነው ሲሉ አዳምጫለሁ። እኔ በ2019 ፅፌያለሁ። ለአፍሪካም እንደሚያሰጋም።
• ደጉ ሳተናው ለጥፎት ከ400 እስከ 600 ሰው ሼር አድርጎታል። በ2019 ነው የተጻፈው። አንቱ የተባለው ሚዲያ ሆነ ተንታይ አሁንም „ተረኝነት“ እያለ ያሽሞነሙነዋል የገዳን ወረራ። እኔ ግን በ2019 ይህን ጽፌያለሁ። ልባም ሰው ግብቶ ብሎጌ ላይ ማንበብ ይችላል።
2019 ዲሴምበር 16, ሰኞ
ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።
ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም። ከዚያ የከበደ መከራ ላይ ናቸው አላዛሯ ኢትዮጵያም ሆነ እማማ አፍሪካም።
ይህ ያን ጊዜ የተጻፈ ነው። ገናም ገና … ጦርነቱ ላዛ ግርዶሽ ነው። የሽብሩ ሱናሜ ለዛ ግርዶሽ ነው። ገና ምን ታይቶ …
“ተረኝነት” የሚለው እጭ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ነው። ተጋድሎውንም ያስተኛው ይኽው ነው። ለዚህ የባልደራሱ አቶ ገለታው ዘለቀ ሰፊውን ድርሻ ተወጥቷል። ያው ከውጭ የሄደው የገዳ ልዐልት እና መሳፍንት ተልዕኮው ይኸው ነው። በ ኢትዮጵያኒዝም ዝም ኦሮሙማን የበላይ እድርጎ ማስቀጠል።
ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ተንታኞች ሚዲያወች በፍፁም ከወሳኙ አስኳላዊ ዕውነት ሊነሱ አልቻሉም። ገናም ገናም። ይህ የእከሌ ተከሌም አይደለም። የሁሉም ችግር ነው። ድህነት።
ወይ አልገባቸውም። የገባቸው እንደ ገዳ ገለታው ዘለቀ ዓይነቶች በዕውነት ላይ አድፍጠዋል።
Filed in: Amharic