>

ይህ ሠራዊት ማለት... (አሳዬ ደርቤ)

ይህ ሠራዊት ማለት…

አሳዬ ደርቤ

➜የመንግሥት አካላት “አያ ጅቦ” መጣልህ እያሉ ዜጎችን እንደ ሕፃን ልጅ የሚያስፈራሩበት፥
➜ለኢትዮጵያውያን እንጂ ለብልጽግናዎች የስጋት ምንጭ ያልሆነ፥
➜”እኛ ከወረድን የባሰ ይመጣል”  በሚል ምክንያት የሥልጣን እድሜያቸውን የሚያራዝሙበት፥
➜የገዥው ፓርቲ አመራሮች ከህውሓት ጋር ተባብረው አማራን ማጥፋት ሲፈልጉ የሚጠቀሙበት፥
➜የባለፈውን ምርጫ ያለ ምንም ፉክክር ለማሸነፍ በሃይለኛው የተጠቀሙበት፥
➜ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ሳይሆን ከአማራ እናቶችና ሕፃናት ጋር የሚያጋጥሙት፥
➜ጫና ሲበዛባቸው አሰልፈው ፎቶ የሚያነሱት፣ ቀለል ሲላቸው ደግሞ የሚበትኑት፤
➜ድሮን ሊሸልሙት እንጂ በድሮን ሊመቱት የማይሹት፥
ወዘተ!️
ወዘተ!️
ወዘተ!️
ሼኔ በጃልመሮ ሳይሆን በብልጽግና ባለሥልጣናት  የሚመራ የሽብር ቡድን ነው! ስለሆነም ከዚህ መንግሥት ከአምና የባሰ ቁማር እንጂ ከአምና የተሻለ አገር መጠበቅ አይቻልም!
Filed in: Amharic