>

በድኑ ብአዴን 4,552  የአማራ ልጆችን ማፈኑንና መረሸኑን በኩራት ነግሮናል...!!!  (አቻምየለህ ታምሩ)

በድኑ ብአዴን 4,552  የአማራ ልጆችን ማፈኑንና መረሸኑን በኩራት ነግሮናል…!!! 

አቻምየለህ ታምሩ


ይመዝገብ! 

*…. ብአዴን የሚባለው የፋሽስት ወያኔ ነውረኛ ድርጅትና የዐቢይ አሕመድ የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ አተላ ተሸካሚ 4,552 የሚሆኑ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆችን ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ብቻ ማፈኑንና መረሸኑን ዛሬ በኩራት ነግሮናል።

እነዚህ ብአዴን የሚባለው የፋሽስት ወያኔ ነውረኛ ድርጅት በግፍ ያፈናቸውና በጭካኔ የፈጃቸው ፋኖዎች በነውረኛው ድርጅት መንገድ መሪነትና መረጃ አቀባይነት ፋሽስት ወያኔ በወሎ፣ በጎንደርና በሸዋ ያካሄደውን የፍጅትና የውድመት ወረራ ደምና አጥንት በመክፈል የተጋፈጡ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው።

ብአዴን የሚባለው የፋሽስት ወያኔ ነውረኛ ድርጅትም እነዚህ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች በጅምላ ያፈናቸውና በግፍ የጨፈጨፋቸው የመንፈስ አባቱን ፋሽስት ወያኔ በአማራ ሕዝብ ላይ ባካሄደው ውድመትና የፍምላ ፍጅት ካለመርካቱ የተነሳ ፋሽስት ወያኔ በአማራ ላይ ተጨማሪ ውድመትና ፍጅት አድርሶ  ነውረኛው ብአዴን ጥማቱን እንዳይቆርጥ ፋኖዎቹ እንቅፋት ስለሆኑበት ነው።

አማራን ለመብላት የተፈጠረው ብአዴን የሚባለው የአማራ ነቀርሳ ዛሬ ላይ በኩራት እየነገረን ያለው የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች አፈና ነገ በጋራ ለፍርድ የሚቀርቡበት የተከፈተ መዝገባቸው ነው!

የነውረኛ ድርጅት ምንደኞች በሙሉ አተላ የሚያሸክማቸው የዐቢይ አሕመድ የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ ነገ ሲወገድ ዛሬ በኩራት እየነገሩን ያሉት ባአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች  ላይ እያካሄዱት ያለው የግፍ አፈናና የጭካኔ ግድያ ፍርዳቸውን የሚያገኙበት ዶሴ ይሆናል!

Filed in: Amharic