>

‹‹የማን ቤት ፈርሶ፣ የማን ሊበጅ.....››

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! የደም መሬት! Bombard the Orommuma Headquarter!››

( ክፍል አንድ)  

ፂዮን ዘማርያም (ኢት-ኢኮኖሚ /ET- ECONOMY)

‹‹የኦሮሙማን ጠቅላይ ጦር ሠፈር አውድም!!! Bombard the Orommuma Headquarter!!!››

‹‹የማን ቤት ፈርሶ፣ የማን ሊበጅ

የአውሬ መፈንጫ፣ ይሆናል እንጅ››

የደም መሬት፡የአማራ ፋኖ  በኦነሬል አብይ አህመድ የኦህዴድ ብልፅግና የስድስት አመት የግፍ አገዛዝ የመሬት ቅርምት መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ የተዘረፈ የህዝብ የመሬት ኃብት

(1) በታከለ ኡማ አትላስ አካባቢ የተሠራ ግዙፍ ህንፃ፣

(2) አዳነች አቤቤ በቤተሰቦቾ ስም አጥራ ያስቀመጠችው ትልቅ መሬት

(3) ግሩም ጫላ የሚዲያ ዋና መስሪያቤት ብሔራዊ ትያትር አካባቢ የሚሠራ ታጥሮ  የተቀመጠ ቁልፍ ቦታ

(4) ሽመልስ አብዲሣ ከወንድሞቹ ጋርታጥሮ የተቀመጠ ሰፍ ቦታ

(5) የኮነሬል አብይ የሥርዓቱ ጀነራሎች የተሸለሙት የደም መሬት በአራብሳ፣ ኮልፌ፣ አያት፣ ቦሌ፣ ንፋስ ስልክ ወዘተ የተሰጣቸው ከአንድ ሽህ አምስት መቶ እስከ ሦስት ሽህ አምስት ሜትር ካሬ ቦታዎች በአማራ ፋኖ አዲስ ስር ነቀል ለውጥ በህዝብ ኃብትነት ወደ መሬት ባንክ ገቢ ይደረጋል፡፡ ይህን መሬት የሚሸጥና የሚገዛ ተጠያቂ እንደሚሆን መግለጫ ተሰጥቶል፡፡  በኮነሬል አብይ የኦሮሙማ ሥርዓት በአዲስ አበባ ከተማ በፈረሰው የደሃ መሬት ላይ መሬቱን ገዝቶ የገነባ ባለጊዜ ሁሉ ለፍርድ ይቀርባል፣ ፍትህና ርትህ ዳግም በሃገሪቱ ያብባል፡፡ ማንም ሰው ከህግ በላይ መሆን አይችልም፡፡ ፒያሳና አራት ኪሎን አፍርሶ፣መሬቱን መዝረፍና መቀራመት አይቻልም፡፡ በኢትዮጵያ ምድር የህግ ሉዓላዊነት ይሰፍናል!!! 

• • •

{1} ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለልቻ፣ ቦሌ አትላስ አካባቢ ሁለት ቦታ /ቱርክ ግቢ ውስጥ 1500ካሜና 2000ካሜ 

{2} ጀነራል አበባው ታደሰ አስረስ ቦሌ 2000ካሜ    

{3} ጀነራል ጌታቸው ጉዲና ሰልባና፣ ንፋስ ስልክ 2000ከሜ

{4} ጀነራል ሀሰን ኢብራሂም ሙሳ፣ ንፋስ ስልክ 2000ከሜ 

{5} ጀነራል ባጫ ደበሌ ቡታ፣ ኮልፌ 2000 ካሜ 

{6} ሌ/ጀኔራል ሹማ አብደታ ሃካ፣ ቦሌ 1500 ካሜ    

{7} ሌ/ጀኔራል አለምሸት ደግፌ ባልቻ፣ ቂርቆስ 1500ካሜ 

{8} ሌ/ጀኔራል ይመር መኮንን፣ ኮልፌ 1500 ካሜ     

{9} ሌ/ጀኔራል አስራት ዴኔሮ፣ ንፋስስልክ 1500ካሜ

{10} ሌ/ጀኔራል ሰለሞን ኢተፋ ሰሙ፣ ንፋስስልክ 1500ካሜ       

  {11} ሌ/ጀኔራል ደስታ አብቾ፣ ቂርቆስ 1500 ካሜ

{12} ሌ/ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ኞጵ፣ ቦሌ 1500 ካሜ 

{13} ሌ/ጀኔራል ጥጋቡ ይልማ ወንድም ሁነኝ ንፋስስልክ 1000ካሜ

{14} ሌ/ጀኔራል መሰለ መሠረት ተገኝ፣ ንፋስስልክ 1500ካሜ  

{15} ሌ/ጀኔራል ደሳለኝ ተሸመ አብተው፣ ኮልፌ 1500ሜካ

{16} ሌ/ጀኔራል አጫሉ ሸለመ መርጋ፣ ኮልፌ 1500 ሜካ      

{17} ሌ/ጀኔራል መሃመድ ተሰማ ገረመው፣ ቦሌ 1500 ሜካ 

{18} ሌ/ጀኔራል ዘውዱ በላይ ማለፍያ፣ ኮልፌ 1500 ሜካ     

{19} ሌ/ጀኔራል በላይ ስዩም አከለ፣ ኮልፌ 1500ሜካ

{20} ሌ/ጀኔራል ብርሃኑ በቀለ በዳዳ፣ ንፋስስልክ 2000ካሜ   

  {21} ሌ/ጀኔራል አሰፋ ቸኮል እንዳለው፣ ቦሌ 1500ካሜ

{22} ሌ/ጀኔራል አብዱራሃማን እስማኤል አሎ፣ ንፋስስልክ 1500ካሜ

የአማራ ህዝብ ከበባና አፈና ከተቀረው ዓለም “The Amhara people are under siege” 

የኮነሬል አብይ አህመድ ኦህዴድ ብልፅግና የግፍ አገዛዝ ባወጀው የአስቸ ጊዜ አዋጅ፣ የኮማንድ ፖስቱ ሠራዊት የአማራ ክልል የትራንስፖርት አገልግሎት በማገድ  መንገዶችን ሁሉ በመዝጋት blockading the road  የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትና የሸቀጣ ሸቀጦች ግብይትን በማስተጎጎል አግደዋል፡፡ በሁለተኛ ጊዜ የአማራ ክልል ላይ በተጣለው ‹‹የአስቸ ጊዜ አዋጅ››  የኮማንድ ፖስቱ ‹‹ኮሬ ነጌኛ›› ገዳይ ቡድን የአማራ ህዝብን በከበባ ሰንጎና አፍኖ የመግደል  ዘመቻ ህዝቡ እንዲቸገር በማድረግ  ላይ ይገኛል፡፡ በአማራ ክልል የህክምና አገልግሎት እንዲቆረጥ በመድረግ የታመሙ ሰዎች ህክምና እንዳያገኙና ወደ ከፍተኛ ሆስፒታሎች ወደ አዲስ አበባ ከተማ ወይም ወደ ደሴ ከተማ እንዳይጎጎዙ የትራንስፖርት እገዳ በመጣል፣ መንገዶቹን በመዝጋት ኮማንድ ፖስቱ አውጆል፣ ስለዚህ ለበሽተኛች የሚሆን መድኃኒት እንዳይገባላቸው በማድረግ ህመምተኞች እንዲሞቱ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ኮነሬል አብይ አገዛዝ ዘመን የዜጎች የመዘዋወር መብትና ነፃነት ተጥሶል፡፡ ከአማራ ክልል ደሴ፣ ደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ መግባት ታግዶል፡፡ የአማራ ህዝብ ለህክምና፣ ለትምህርት፣ ለሥራ፣ ለንግድ ከጎጃም ወደ አዲስ አበባ መግባት ተከልክሎል፡፡ የትግራይ ተጋሩዎች ወደ አዲስ አበባ በአይሮፕላን እንዳይገቡ ታግደዋል፡፡ የጎሙ ተወላጆች ከአዲስ አበባ ወደ አርባ ምንጭ በጉልበት ተጭነው ተወስደዎል፡፡

  • ‹‹በሽፍትነት ሪቤልስ በሚመስል ነገር ከእንግዲህ በኃላ የኢትዮጵያ መንግሥትን መጣል ሳይሆን መነቅነቅ አይቻልም!!!›› ኮነሬል አብይ አህመድ
  • ‹‹የኦሮሞ ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል›› ሽመልስ አብዲሳ
  • ‹‹አማራን እንደ ትግራይ እንቆልፋለን!!!›› ዳንኤል ክብረት
  • ‹‹ፋኖ ለድርድርም ለግርግርም አይመችም!!! ›› ኮነሬል አብይ አህመድ
  • ‹‹ክልል ለሽፍታ አምነን አንሰጥም፣ ባይሆን ወረዳ እንሰጣለን!!!››
  • ‹‹ጫካ ውስጥ የተንጠለጠለ ቆንጣ ናፈቃቸው እንጂ፣ የእርሻ መሬት ስጥተናቸው ነበር!!!›› አረጋ ከበደ
  • ‹‹አመራሮቹን እየደመሰስን ነው፡፡ ከዚህ በኃላ ፅንፈኛውን ማጥፋት አያቅተንም፡፡›› ብርጌደር ጀነራል አዲሱ መሃመድ
  • ‹‹ምን ዋጋ አለው ይህን የሚመስል አብረቅራቂ ህንፃ ሠርተን ከጎኑ ያለው ግን አበላሸብን፣ አሳጣን፣ ድሪቶ አለብን ስለዚህ ይህን ደሞ በጊዜ ብናነሳው ምንነው፡፡›› ግርማ ሠይፉ የአዲስ አበባ የከተማ አስተዳደር ኢንቨስትመንት ኃላፊና አጋር ፓርቲ የካቢኔ አባል፡፡ 
  • ‹‹አሣማ ከመሆን አንበሳ መሆን መርጫለሁ!!!›› ፋኖን የተቀላቀሉት ጀነራል

‹‹የኦሮሞ ህዝብ ከቀየው አዲስ አበባ መግፋትና ማሳደድ አክትሞለታል›› ሽመልስ አብዲሳ

የአዲስ አበባ የቤትና ህንፃ ፈረሳ፡- በተለይም እድሜ ጠገብ የሃገሪቱ ቅርስ የነበሩ ቤቶችን ህዝብን ሳያማክሩ አፍርሰውታል፡፡ መርካቶ፣ ፒያሳ፣ አራት ኪሎ፣ ሜክሲኮ፣ ሠንጋ ተራ፣ ካዛንችስ፣ ሾላ፣ ብሔራዊ ትያትር፣ ለጋህር፣ ቄራ፣ ቦሌ፣ መገናኛ ወዘተ  እልቆ መሳፍርት ቤቶችና ህንፃዎች ፈርሰዋል፡፡ ፒያሳ አካባቢ የአራዳ ህንፃዎችና እንዲሁም እየሩሳሌም መታሰቢያ ህንፃ ያለ አንዳች ምክንያት አፈረሱት፡፡ ቴድሮስ አደባባይ ከፍ ብሎ የሚገኘው አንበሳ መድኃኒት ቤትና በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሲኒማ ቤት ‹‹ሴጣን ቤት›› አፈረሱት፣ ብሔራዊ ትያትር አካባቢ መከላከያ ሚኒስትር ጎን ኢትዮጵያ ሆቴል አጠገብ የነበረውን ህንፃ አንበሳ ሻይ ቤት አፈረሱት፡፡ ለገሃር የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ህንጻ ወዘተ ይገኙበታል፡፡ 

‹‹በኮሪደር ልማት ስም የሚደረገው ነባር መንደሮችን እያፈረሱ በአዲስ ግንባታዎች የመተካት እንቅስቃሴ፣ የአዲስ አበባን አሻራ ሊያጠፋ እንደሚችል እናት ፓርቲ አስታወቀ፡፡ በልማት ስም የቀደመ ታሪክንና የቀደመው ትውልድን አሻራ የማጥፋት ዘመቻ እየተካሄደ ነው ሲልም፣ ፓርቲው ዓርብ መጋቢት 13 ቀን 2016 .. ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ፒያሳን ጨምሮ በተለያዩ የከተማዋ ነባር ሠፈሮች፣ ነባር ሕንፃዎችና ቤቶች መፍረሳቸው፣ ከታሪክ አንፃር ብቻ ሳይሆን ዘርፈ ብዙ ጉዳት እንዳለው በመግለጫው አትቷል፡፡ ‹‹አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ እናደርጋታለን›› በሚል የአዲስ አበባ ከተማ መገለጫ የሆኑ አሻራዎች መውደማቸው ጥፋት መሆኑን ገልጿል፡፡ 1900ዎቹ ጀምሮ ተገነቡ የሚላቸው (1) የአበበች ጎበና መኖሪያ፣ (2) የቢትወደድ ኃይለ ጊዮርጊስ አግደው መኖሪያ፣ (3) የብሪቲሽ ባይብል ሶሳይቲ፣ (4) የመሐመድ ዓሊ መኖሪያ፣ (5) የሙሴ ሚናስ ኬርቤኪያ መኖሪያ፣ (6) የማቲግ ኬቮርኮፍ መኖሪያ፣ (7) የአህመድ ሳላህ (ሻሺብ ሀይሴት) መኖሪያ፣ (8) የአልፍሬድ ኢልግ መኖሪያ፣ (9) የአርቲን ኢቫኪያን መኖሪያ፣ (10) የአጋፋሪ ከልሌ መኖሪያ፣ (11) የጳውሎስ ኮርዳስ መኖሪያና ሌሎችም ታሪካዊ ኪነ ሕንፃዎች ለውድመት ተዳርገዋል ሲል በስም ዘርዝሯል፡፡ የኮሪደር ልማቱ እነዚህን ታሪካዊ የከተማ አካባቢዎች በቅርስነት በመከለል ለከተማው ማስገኘት የሚቻል ከፍተኛ የቱሪዝም ገቢን እንደሚያሳጣ፣ ይህን መሰሉ በልማት ስም የሚደረግ ነባር መንደሮችን እያፈረሱ በአዳዲስ ግንባታዎች የመተካት ሥራ፣ ታሪክ አልባ ከተማን ሊያሳቅፈን ይችላል ሲል እናት ፓርቲ ሥጋቱን በመግለጫው ገልጿል፡፡››

‹‹የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተተኪ መሬት ሳይሰጠው 980 የሚጠጉ ቤቶች እንዳፈረሱበት ተገለጸ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 18 መደበኛ ስብሰባውን ማክሰኞ መጋቢት 9 ቀን 2016 ሲያደርግ አቶ ፈይድ ሸራብ የተባሉ የምክር ቤት አባል እንደገለጹት፣ የኮርፖሬሽኑ ንብረት የነበሩትን ቤቶች የከተማ አስተዳደሩ ካፈረሰ በኋላ፣ ተጨማሪ ለመገንባት የሚያስችል ተተኪ መሬት አለመሰጠቱን ገልጸዋል፡፡››

የሸገር ከተማ ፕሮጀክት፡ የኮነሬል አብይ የኦሮሙማ የእጅ አዙር አገዛዝ፣  የአዲስ አበባ ከተማ ላይ ተቆርሷ የተሠጠ የሸገር ከተማ 1600 (አንድ ሽህ ስድስት መቶ) ስኩየር ኪሎሜትር ወይም 1600 000 000 (አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሚሊዮን) ካሬ ሜትር ቦታ  ህገመንግሥቱን በጣሰ መንገድ ተዘርፎል፣ ህዝብ ያላማከረና 600000 (ስድስት መቶ ሽህ) ሰዎችን በግፍ ያፈናቀለ የኦሮሙማ አገዛዝ ያለአንዳች ማስተር ፕላን ጥናት በኦህዴድ ብልጽግና ዘረኛና ተረኛ የኦሮሙማ ሥርዓት የከተማ ህዝብ ንቅለ ተከላ የተከናወነበት ዘመን ነው፡፡ ማንነት ተኮር በአማራነታቸው ምክንያት የተፈላቀሉ ዜጎች ቤትና ንብረት በኮሬ ነጌኛ ሽመልስ አብዲሳ ቀጭን ትእዛዝ የፈረሱ ቤቶች ላይ የተገነቡት ህንፃዎች የፍርድ ቀን ሲመጣ የመሬታቸውን ዋጋ ከነወለዱ ከተለዋጭ ቦታ ጭምር እንደሚካሱ ምንም ጥርጥር የለንም፡፡ እነ ኮነሬል አብይ አህመድ፣ ሽመልስ አብዲሳ፣ አዳነች አቤቤ ኢትትዮጵያ ውስጥ ለፍርድ ይቀርባሉ፡፡ ዘረኛ አፍራሾች ገንቢዎች ሊሆኑ አይችሉም!!! ሰው ሰው ያልሸተተ ልማት ለጥፋት እንዲሉ በፋሽስቱ ሽመልስ አብዲሳ በኦህዴድ ብልፅግና የተገነቡ ሁሉ የህዝብ ኃብት ይሆናሉ!!! 

(1) የኦሮሞ ሥነጥበብና ማሠልጠኛ ማዕከል፣ (2) የኦሮሞ ባህላዊ ምግብ ማዕከል፣ (3)ኦሮሚያ ባህላዊ ግብይት ማዕከል፣ (4) ኦሮሚያ ባህላዊ እቃዎች፣ (5) ስንቄ ባንክ፣ (5) ጋዲሳፋ ህንፃ (ጎኖፋ ኦሮሚያ) (6) የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የፕሬዜዳንት ቢሮ፣  (7) ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ህንፃ፣ (8) የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንፃ፣ (9) ኦቢኤን ሚዲያ ኮምፕሌክስ ህንፃ፣ (10) ኢንትሮዳክሽን ኦሮሚያ ህንፃ፣ (11) ልዩ ልዩ መንግሥታዊ ሚዲያና ኢንተርፕራይዝ ህንፃዎች ይገኙበታል፡፡ ከኦቦ ሽመልስ አብዲሳ በይፋ ማህበራዊ ገፃቸው ካሰፈሩት የተወሰደ፡፡ Among these are the projects: Oromo Arts Training Center, Oromo Cultural Food Center, Oromia Cultural Marketing Center, Oromiya Cultural Materials, Sinqe Bank, Gaddisafa Building (Gonofa Oromia), Office of the President of Oromia Regional State, Oromia Police Commission, Oromia General Court, OBN Midea Complex, Introduction of Oromia. Different government media and enterprises

ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ኃይል፡

ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ኃይል ፡- የህህብ መከታና ኃሌንታ የሆነው ሠራዊት ከህዝብ ጎን መቆም አለበት፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ግብር ከፍሎ ያስተማረህ፣ ያሠለጠነህና ደሞዝ የሚቆርጥልህ የሃገር ድንበር እንድትጠብቅ የገባህውን ቃል-ኪዳን መርሳት የለብህም፡፡ አንድ ሃሙስ የቀረው የኮነሬል አብይ አህድ መንግሥት  የኦህዴድ ብልጽግናን የኦሮሙማ ሥርዓትን ለመዘርጋትና ሃገሪቱን ወደ  አስራስደተኛው  ክፍለዘመን  ለመመለስ አቅዶል፡፡ ዴሞክራሲን በገዳ ሥርዓት ለመተካት፣ የሌላ  ኃይሞኖተኞችን  እምነት ተከታዩን ሁሉ በዋቄ ፈታ እምነት ለማጥመቅ፣ የኦሮሙማ መንግሥት ለማቆም ኢትዮጵያን የማፈራረስ እቅድ ነድፎ በመፈፀም ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ወታደር ይሄን ለማስፈፀም ቃል ኪዳን አልገባም፡፡ ስለዚህ ከጭቁኑ ሰፊ ህዝብ ጋር በማድረግ አፈሙዝህን በኢህዴድ ብልጽግና ላይ በማዞር የአማራ ፋኖን በመቀላቀል በሚመሠረተው የሽግግር መንግሥት ተዋናይ በመሆን ጭቁኑን ወታደር በመወከል ተሳታፊ መሆን ታሪክ የጣለችብህ አደራ ነው፡፡ ለሃገሪቱ ህዝብ በገባው ቃል- ኪዳን መሠረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ኃይል የብሔር ወገንተኛነት የለውም፣ የኃይማኖት ወገንተኛነት የለውም፣ የፖለቲካ ወገንተኛነት የለውም፡፡ የሠራዊቱ ጀነራል መኮንኖች የአዲስ አበባን የደም መሬት ከደሃው ህዝብ ላይ በመዝረፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ጀነራል መኮንኖቹ የኮነሬል አብይ ብልፅግና መንግሥት ፓርቲ ተመልምለው ጥቅማቸውን በማግበስበስ ላይ ይገኛሉ፣ መቶና ሁለት መቶ ሚሊዮን ብር የሚሸጥ መሬት ተሸልመዋል፣ ሁለትና ሦስት ቪ8 መኪኖች ተሰጥቶዋል፣ የኪራይ ቤት ተሰጥቶቸዋል፣ ከፍተኛ ደሞዝ ይከፈላቸዋል፡፡ ጀነራል መኮንኖቹ ሠራዊቱን ለማያባራ ጦርነት ውስጥ ከተውታል በትግራይ ክልል የሁለት አመታት ጦርነትና በአማራ  ክልል አንድ አመት ሊሞላ ወራቶች የቀሩት ጦርነት ጨቁኑን ወታደር ከህዝብ ጋር በማዋጋት ላይ ይገኛሉ፡፡ ጭቁኑ ወታደር የህዝብ ልጅ ነውና ከህዝባዊ ትግሉ ጋር በመቀላቀል ከአማራ ፋኖ ጋር ማበር ለቀጣዩ ህይወታችሁ በሠራዊቱ ውስጥ ለመቀጠል ዋስትና ጣገኛላችሁ፡፡  የኮነሬል አብይና ሽመልስ አብዲሳ ፋሽታዊ ሥርዓተ በኦሮሞ ህዝብ ስም በመሬት ዘረፋ፣ በወርቅ ዘረፋ፣ በዶላር ዘረፋ ላይ ይገኛሉ፣ ሃገር ዘርፈው ለመኮብለል አቅደዋል፡፡ የአብይ መንግሥት አክትሞለታል፣ የኦሮሞን ህዝብ እንዲጠላ ለማድረግ አንዴ ከአማራው፣ አንዴ ከትግራዋይ፣ አንዴ ከደቡብ ህዝብ ወዘተ ሲያጋጨው ስድስት ዓመታት ተቆጥሮል፡፡  የኦሮሞ ህዝብ፣የኦሮሞ ቄሮ፣ ከአማራ ወንድሞችህ ጋር በጋራ በመታገል በትረ መንግሥቱን ለመጨበጥ ታገል፡፡ በስምህ የሚምለውንና የሚገዘተውን የኮነሬል አብይ መንግስት አስወግድ፣ ከአማራ ፋኖ ጋር አብር፡፡  የትግራይ ህዝብ ወያኔን አስወግደህ ከኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ጋር ተቀላቀል፣ የወያኔን የግፍ አገዛዝ በህዝባዊ አመጽ አስወግድ፡፡  

 

የታሠሩት የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ!!!

የቤት ማፍረስ ዘመቸው ይቁም!!

Filed in: Amharic