ሀብታሙ አያሌው በኩላሊት ጠጠር ታመመ [ኤሊያስ ገብሩ]

Habtamu Ayalew Andinetየቀድሞ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረው ሀብታሙ አያሌው፣ በኩላሊት ጠጠር መታመሙ ታውቋል፡፡ በዛሬው ዕለት ዘውዲቱ ሆስፒታል ለህክምና መምጣጡ የተረጋገጠ ሲሆን፣ የህክምና ምርመራ ያደረገለት ዶ/ርም፤ ሀብታሙ በሁለቱም ጎኑ በኩላሊት በጠጠር ችግር ሳቢያ መታመሙን እንደገለጸላት ባለቤቱ ወ/ሮ ቤተልሄም ተናግራለች፡፡ ሀብታሙም ላጋጠመው ህመም ምርመራ ተደርጎለት እና መድሃኒት ተሰጥቶት በአሁኑ ሰዓት ወደቂሊንጦ እስር ቤት ሊመለስ መኪና እየጠበቀ መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.