>

ዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ለዛሬ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ተጠይቆባቸው የነበረው ሶስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ማህሌት ፋንታሁን በፍቃዱ ሃይሉ እና አቤል ዋበላ ላይ ተጨማሪ 28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ ፓሊስ የጠየቀው 28 ቀን የተፈቀደለት ሲሆን ማንም የቤተሰብ አባል ችሎቱ ውስጥ ያልተገኘበት ዝግ ችሎት ነበር፡፡

ጦማርያኖቹ ለደቂቃዎች ችሎቱ ውስጥ ቆይተው ከመውጣታቸው በፌት ጊቢ ውስጥ ያሉ ቤተሰብ ጓደኞች ዲፕሎማቶች እና ሌሎች ሊከታተሉ የመጡ ሰዎችን ከግቢው አንዲወጡ ፓሊስ አስገድዷል፡፡ በዚህም የተነሳ ወደ “ፍርድ ቤት” ጊቢው ሲገቡ አንጂ ሲወጡ ቤተሰብና ወዳጅ ሊያያቸው አልቻለም፡፡ በዛሬው ችሎት ቤተሰብ አባላት ላይ ከፍተኛ ወከባና እንግልት የደረሰ ሲሆን ብዙ የቤተሰብ አባላትና የቅርብ ጓደኞች ሲያለቅሱ ታይተዋል፡፡

ማህሌት አቤልና በፍቃዱ በጠንካራ መንፈስ ላይ ሆነው የታዩ ሲሆን 28 ቀን መፈቀዱም ክሳቸው በጸረ ሽብር ህጉ እንደሚታይ ያመለክታል፡፡

የዞን9 ጦማሪያን ጓደኞቻችን ምንም አይነት የወንጀል ተግባር ላይ ተሰማርተው እንደማያቁ እና ክሳቸው ፓለቲካዊ እንደሆነ እያስታወስን በፍርድ ቤት ተገኝተው አጋርነታቸው ላሳዩ ከ120 በላይ ለሆኑ የዞን ዘጠኝ ወዳጆች ልባዊ ምስጋናችንን በታሰሩ ጓደኞቻችን ስም እናቀርባለን!

‪#‎FreeZone9bloggers‬ ‪#‎FreeEdom‬ ‪#‎FreeTesfalem‬ ‪#‎FreeAsemamaw‬‪#‎Ethiopia‬

የዞን ዘጠኝ 

Filed in: Amharic