>
5:21 pm - Saturday July 19, 1749

በሳውዲ ጉዳይ  እንደ ተወካዮቻችን ሳውዲዎች አልበደሉንም‼ (ነቢዩ ሲራክ)

በሳውዲ ጉዳይ 

እንደ ተወካዮቻችን ሳውዲዎች አልበደሉንም‼

ነቢዩ ሲራክ

* ስለ ስደተኛው እናብራለን   ‼
   በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊው ስደተኛ በወህኒና ከወህኒ ውጭ ስቃይ መከራው በዝቶበታል። ወገን በግፍ ታስሮ ምግብ ውሃ እና ህክምና  ያገኝ ዘንድ ሰብአዊ መብቱን የሚያስከብር ተወካይ አጥቷል።
  ኩሩው ዜጋ ተንቋል። ከክቡሩ የሰው ልጅ የተፈጠረ መሆኑን የዘነጉት ሳውዲዎች ብቻ አይደሉም። ለመብቱ መከበር ቆምን የሚሉ የኢትዮጵታ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና  የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኤጀንሲን ሰውነቱን ረስተውታል ፣ ዘንግተውታል ብቻ ሳይሆን ጨክነውበታል  🙁 ለስደተኛው ዜጋ መብት  የተቋቋሙት ተቋማቱ ሀገር ወዳድ ፣ ወገን አጉራሽ ደጋፊ ዜጋውን ዶላር አያመጣም  ብለው ዘንግተውታል …
   አዎ እውነት እላችኋለሁ ሳውዲዎች እንደ እኛ ሹሞች አልከፉብንም ። እናም ለምን ስደተኛው ተዘነጋ ብለን ከዚህ በኋላ ደረቅ የተደበቀውን እውነቱን እንናገራለን ። ልዩነት ካለን ከማንኛውም አካል ጋር በአጋርነት በመጓዝ ስለ ስደተኛው መገፋት ድምጽ ከሚያሰሙት ጎን ሆነን የተገፊ ወገኖቻችን በደል መከራና ስቃይ ለአለም እናደርሳለን ።
አዎ ዝም አንልም  ‼
የካቲት 3 ቀን 2014 ዓም
Filed in: Amharic