>
5:13 pm - Friday April 18, 9766

የካድሬዋ የግል ማስታወሻ ካላበጣበጥንና ካልበጣጠስን እኛ ሁሌም ሰላም አይኖረንም!!! (ሰናይት መብራህቱ)

የምንደኛ ብሎገሮች ስብሰባ በሕወሓት ልዩ ዞን አደረጃጀት አዲስ አበባ 03/07/2010.
በጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን ላይ ሕወሓት አቅዋም ስልትና ስትራቴጂ
አቁዋም:-
1. የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን ፈጽሞ ከኛ ቁጥጥር ውጪ መሆን የለበትም። ደማችንን አፍስሰን ያገኘነውን ማንም ንግግር ስላሳመረ መውሰድ የለበትም።
2. የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን እኛ ባንይዘውም እኛ የምንቆጣጠረው በኛ ብቻ የሚተማመን ደካማ ሰው ነው መያዝ ያለበት ። 3. ባሁኑ ሰዓት ትግራዋይ በሃገሪቱ የኢኮኖሚ የበላይነት እየያዘ ይገኛል። አሁን ባለው መረጃ መሠረት ትግራዋይ ከሃገሪቱ ሃብት 70 በመቶ መቆጣጠር ችሏል። ግባችን ትግራዋይ ከሃገሪቱ ሃብት 85 በመቶ እንዲቆጣጠር ማድረግ ነው። የፖለቲካ የበላይነት የኢኮኖሚ የበላይነትን ተከትሎ ይመጣል። ይህ ሊሆን የሚችለው ጠንካራ ሕወሓት ሲኖርና ዋና ዋና ሥልጣን መቆጣጠር ሲችል ነው። ስለዚህ የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን ከኛ ቁጥጥር ውጪ ከሆነ የያዝነው የኢኮኖሚና የፖለቲካ የበላይነት ዋስትና አይኖረውም ማለት ነው ። ዋስትና አይኖረውም ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱ ትግራዋይ ለአደጋ ይጋለጣል። እስካሁን ያካበትነው ሀብትም ሊወረስ ይችላል። ስለዚህ ሥልጣኑ ከኛ ቁጥጥር ዉጪ ሆኖ ትግራዋይ ለአደጋ ከሚጋለጥ ድርጅቱም ኢህወዴግ ቢፈርስ ይሻላል።
4. ኦሮሞ ብዛት ያለው በራሱ የሚተማመን ሕዝብ ስለሆነ በፍጹም የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን መያዝ የለበትም። እርስ በራሱ ስምምነት ሊኖረው አይገባም። እነሱ ከተስማሙ የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ ።አሁን የጀመርነው ኦህዴድን የማፍረስና ለኛ የሚመች ሌላ ኦህዴድ የመፍጠር ግባችን የሚሳካውም ኦሮሞ ከዋና ዋና ሥልጣን ከራቀ ብቻ ነው ። አሁን ያሉት የኦህዴድ አመራሮችም ገለል መደረግ አለባቸው።የማያርፉ ከሆነ ማሳሰር ነው።
5. አማራም ቢሆን ብዛት ስላለው በአፍ ከኛ ጋር ያለ ቢመስልም ውስጡ ስለማይታመን በፍጹም የጠቅላይ ሚኒስትር መያዝ የለበትም ። እነሱ የድሮውን ኢትዮጵያ መመለስ ብቻ ነው ሕልማቸው። ትምክህት። አሁን እንደምንም በጥንቃቄ ይዘን የፈታነው የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይም ከእንደገና ሊያገረሽ ይችላል። ስለዚህ ኦሮሞና አማራ ሥልጣን ይዘው የትግራዊያን መብት ለአደጋ ከሚጋለጥና ትግራዋይ ከሚጠፋ ኢህወዴግ ቢጠፋ ይሻላል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን ከእጃችን እንዳይወጣ የመቆጣጠሪያ ስልቶቻችን:-
1. ጠቅላይ ሚኒስትር የሚሆን ሰው ሁልጊዜም በራሱ ከማይተማመን ከአናሳ ብሔር መመረጥ አለበት ።
2. የደህንነት መስሪያ ቤቱ ሁልጊዜም በኛ እጅ መሆን አለበት። ፈጽሞ ከእጃችን ሊወጣ አይገባም። እዚህ ላይ የሞት ሽረት ትግል ነው መደረግ ያለበት።
3. የመከላከያ ሚኒስቴር ሁልጊዜም እኛ የምንቆጣጠረው ከአናሳ ብሔር መሆን አለበት።
4. ባሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ምርጫ 45ቱ የኛ የህወሓት/ኢህወዴግ ምክር ቤት አባላት ሙሉ ድምፃቸውን ለአቶ ሽፈራው ሽጉጤ መስጠት አለባቸው። ይህ የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። እዚህ ላይ አንድም አባል ስህተት መፈጸም የለበትም። ይህ ትግራዋይ ሁሉ የጣለብን ግዴታ ነው። ከዚህ ውጪ አማራጭ የለንም። አቶ ሺፈራው እንዲያሸንፍ ማድረግ አለብን። ስለዚህ አቶ ሽፈራው የኛ የህወሓት ኢህወዴግ ምክር ቤት አባላት 45 የተረጋገጠ ድምፅ አለው። በአንደኛም ዙር በሁለተኛም ዙር። ከራሱ ፓርቲ ከደህዴን 20 ድምፅ ብቻ እንክዋን ቢያገኝ ከብአዴንም አንድ ሁለት ቢያገኝ በቀላሉ ወደ ቀጣይ ዙር ያልፋል። በቀጣዩም ዙር በቀላሉ ያሸንፋል። ከኛ 45ድምፅ አስተማማኝ ስላለው ከቀሩት ድርጅቶች የተወሰነ ተጨማሪ ቢያገኝ ያሸንፋል። እኛ ስላስመረጥነው ደህንነቱም በኛ እጅ ስለሆነ ለኛ ይታዘዛል። የጀመርነው ኦህዴድን የማጥራት ሥራ ከኛ ጋር ሆኖ በደንብ ይሰራል ማለት ነው ።
5.ይህ እስካሁን ያልነው እንግዲህ የአጭር ጊዜ እቅድ ነው። ከረጅም ጊዜ አኩዋያ ግን አጋር ድርጅቶችን ወደ ኢህወዴግ መቀላቀልና የብዙ አናሳዎች ድምር ትልልቆቹን ብሔሮች እንዲያሸንፍ ማድረግ ነው። ከዘላቂነት አኩዋያ ይህ ነው የሚያዋጣን።
6. ሌላው በትላልቅ ብሔሮችና በአናሳዎች መሐከል በየቦታው ግጭት መቀስቀስና እንዳይረጋጉ ማድረግ ነው ። ትልልቆቹም በውስጣቸው እርስ በራሳቸው እንዲሁም አንዱ ከሌላው እንዳይስማሙ ትልቅ ሥራ መሰራት አለበት። ትልልቆቹ ከተረጋጉ እኛን ይበሉናል። በዚህ ረገድ በሶማሌ ክልል ጥሩ ሥራ ተሰርቷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ በኩል ያለው ሥራ ግን መንቀራፈፍ ይታይበታል። አሁንም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። በደቡብ በጋምቤላና በአፋር በኩልም የሚሞከር ነገር ካለ መሞከር አለበት። ጊዜ የለንም። ከላበጣበጥንና ካልበጣጠስን እኛ ሰላም አይኖረንም። እያንዳንዱ ትግራዋይ ሴት ወንድ ሁሉ በያለበት ሆኖ ለዚህ የራሱን ድርሻ መወጣት አለበት። ይህ ጊዜ የማይሰጠው የህልውና ጉዳይ ነው። ተግባሩ ግን በጥንቃቄ ነው መፈጸም ያለበት። ባለፈው ቢሾፍቱ ላይ ቄሮን ለመምታት የቀየስነው ስልት ለምንድነው ያለስራው? ከተለያዩ ከተሞች ያሰባሰብናቸው ከሁለት ሺህ የሚበልጡ የደቡብ ክልል ባብዘኛው ወላይታዎች ወጣቶች ከቄሮ ጋር ተቀላቅለው የሚሰሩ መስለው የአማራ ንብረትና የሌሎች ብሔረሰቦች ንብረት እንዲያጠቁ የተደረገው እቅድ ጥሩ ሆኖ አፈፃፀም ልክ አልነበረም። ለዛ ነው ያልተሳካው። ወጣቶቹ ማሰባሰብ የነበረባቸው ከተማ ውስጥ በአጭር ሰዓት ውስጥ ነው እንጂ የተንዛዛ መሆን የለበትም። በፍጥነት መፈጸም ነበረበት። እዛ ላይ ወጣቶችን ማሰባሰብ ረጅም ጊዜ ወስዷል። ከዚህ ትምህርት መውሰድ አለብን። 2000 ወጣት ከተማዋን በአንዴ አመድ ያደረጉት ነበር። ሕዝቡ ደም ሲያይ ስለሚደነግጥ እንዲገደሉ የተፈለጉ ሰዎችንም በዚህ አጋጣሚ መግደል ይቻል ነበር። አሁን ያለው ኦህዴድ መስተዳድር እንዳልቻለ ትልቅ ማሳያም ይህንን ነበር። ለወደፊቱ እንደዚህ ያለ ተልዕኮ ለመፈፀም ጥንቃቄና ፍጥነት ወሳኝ ነው። ዓወዳይ ላይ ጥንቃቄና ፍጥነት ስለነበረ ነው የተሳካው። ስለዚህ ትግራዋይ ሁሉ ንቁ። የአሰቸከወይ ጊዜ አዋጁ የፈጠረልን መልካም ዕድል መጠቀም አለብን። ጊዜ የለንም።

Filed in: Amharic