
እግዚአብሔር ሆይ የተበደሉና በጥልቅ ሃዘን ውስጥ ያሉ ሰዎችን ጩኸት ስማ!!!
በተያያዘ
በአማራ ብሔር ላይ ያነጣጠር ጥቃት ቀጥሏል!?!
ሀንድ ቱ ሀንድ ኢትዮጵያ

በጂማ ሊሙ ዛሬ የሚከበረውን የክርስቶስ እርገት ለማክበር በማታ ወደ ጨንጊ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በመጓዝ ላይ የነበሩ ሦስት የአማራ ብሔር ተወላጆ በገጀራ ታርደው ሕይወታቸው ሲያልፍ አንድ ሌላ በጽኑ ቆስሎ ሆስፒታል ገብቱዋል።
ሲሆን አንድ ሰው በከባድ ጉዳት ሕክምና ገብቷል፡፡ ይህን መሰሉ ጥቃት አዲስ አለመሆኑን ያስታወሱት አክቲቪስቶች በ1999 ዓም በርካታ አማሮች በሻሻ አቦ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በገጀራና በእሳት መገደላቸውን በምሳሌ ጠቅሰዋል።
ትናንት በተፈጸመባቸው የጭካኔ እርምጃ ሕይወታቸው ያለፈው ሶስት ሰዎችን በስም ጠቅሰው ይፋ አድርገዋል። እነዚህም አስማማው አማረ ፣መርሻ መኮንን እና መኳንንት የተባሉ መሆናቸውን ጠቅሰው የቆሰለው ብርሀኑ ጌቱ ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት ደርሶበታል ትብሉዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በቤንሻንጉል ክልል ትልልንት በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ተወጋግቶና ተሰልቦ ጉዳት የደረሰበት የ14 ዓመቱ አቸፈር ላይ ከተወሰደው በተጨማሪ ዛሬም በአማራ ተወላጆች ላይ ድብቅ ጥቃት ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በቀስት እየተወጉ የሞቱና ዐይናቸው የፈሰሰ መኖራቸውን የመረጃ ምንጮቻቸውን ጠቅሰው ጽፈዋል።
ዶ/ር አብይ አህመድ ሁኔታው በአስቸኩዋይ እንዲጣራና ውሳኔ እንዲሰጡ የሚጠይቁም አሉ።