>
5:58 am - Thursday March 30, 2023

በትግራይ  የአቶ መለስ ዜናዊ ቤተክርስቲያን ይታነጻል!?! በአዲስ አበባ  የእመቤታችን ቤተክርስቲያን በፖሊስ ይፈርሳል?!? (ዘመድኩን በቀለ)

 በምሪ ትግራይ ሰውየው አይተ መለስ ዜናዊ ከቅዱሳን እንደአንዱ ተቆጥረዋል። ወዳጄ በትግራይ ምድር ድፍረት እዚህ ጥግ ደርሷል።
~ በቀደመ ጊዜ ቤተክርስቲያን ያሳነጹ ኢትዮጵያውያን ነገሥታት በቤተክርስቲያን ውስጥ የመታሰቢያ ሥዕል ይሳልላቸው ነበር ። ልማድም ነው ። ታዲያ ጋሼ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምን ስላደረጉ ነው እንዲህ በምሥላቸው የተንቆጠቆጠ ቤተክርስቲያን የታነጸላቸው ? ይኼኔ እኮ በሩቅ ቆሞ በቅርብም ሔዶ የሚሳለምም ፣ የሚሰግድላቸውም አይጠፋም።
~ የፈለገው ጥግ ድረስ ቢወዷቸው በቅድስት ቤተክርስቲያን ማላገጥና ማሾፍ አግባብ አይደለም። ነውርም ፣ ኃጢአትም፣ ወንጀልም ነው። ራሳቸው አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት ቢኖሩ እንዲህ ያደረጉትን አመራሮች ሰብስበው ቂሊንጦ ነበር የሚያወርዷቸው። እንዴት ለአልባንያ ኮሚንስቱ አፍቃሪ ቤተመቅደስ ይታነፃል ???
~ ቤተክርስቲያን በዚህ መልኩ ስትደፈር ቅዱስ ፓትሪያርኩም ፣ ሀገረ ስብከቱም ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱም ዝም ብሎ ያያሉ። የጉድ ዘመንና ለጉድ የጎለተን ፍጥረቶች ተገጣጥመን አረፍነው።
በሌላ ዜና ደግሞ ፦
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ስሙ ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የምትገኘውን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ መስተዳድር በግሬደር ፍርስርሷን አውጥቶታል ። ንዋያተ ቅዱሳቱም ሜዳ ላይ ተበትኗል ።
~ አዲዮስ ኦርቶዶክስ አዲዮስ ተዋሕዶ ! 
~ ቅዱስነታቸው ሩሲያ ነው የሚገኙት ። ጠቅላዩ ደግሞ ሳዑዲ አረቢያ። ከግብጽ ጋር ያለው ነገር አላምር ያለው መንግሥታችን ሩሲያን በፓትሪያርኩ በኩል ደጅ እየጠና ነው የሚሉም አሉ።
~ በምሥራቅ አፍሪካማ የሆነ ነገር ይሸታል ። ጠሚዶ ያለ ነገር ሱዳን ፣ ጅቡቲ ፣ ኬንያ ፣ አሁን ደግሞ ሳዑዲ አረቢያ አይንከራተቱም። ደግሞ እኮ በሔዱበት ሁሉ ሀገራቱ እስከዛሬ ያሰሩአቸውን ኢትዮጵያውያን በመፍታት ነው ገጸ በረከት የሚያቀርቡላቸው።
~ በሉ ክፉ አታናግሩኝ ። ደኽና እደሩ ።
~ ነገር ግን የአቶ መለስ ዜናዊን ወርሃዊ ክብረ በዓሉን የምታውቁ ግን አደራ ንገሩኝ። ጧፍ ምናምን ለመላክ ሳይሆ ለጠቅላላ እውቀት ነው ። ስንክሳሩም ውስጥ ገብቶ እንደሁ እባካችሁ አጣሩልኝ አደራ !  አደራ !።
ሻሎም !  ሰላም !
Filed in: Amharic