>
5:13 pm - Sunday April 19, 1063

ከስልጣን የተባረረው የፖሊስ ኮሚሽነር ቀንደኛ ወንጀለኛ ከመሆኑም ባሻገር በቦምብ ጥቃቱ እጁ እንዳለበት መረጃዎች ጠቆሙ። (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ከስልጣን የተባረረው የፖሊስ ኮሚሽነር ቀንደኛ ወንጀለኛ ከመሆኑም ባሻገር በቦምብ ጥቃቱ እጁ እንዳለበት መረጃዎች ጠቆሙ። (ምንሊክ ሳልሳዊ)

የፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ አዲስ አበባና በክልል ሕወሃት በታክሲ ላይ በሬስቶራንት እና በተለያዩ አከባቢዎች የፈጸመችውን ፍንዳታዎች የመራና በግብረ አበርነት የተሳተፈ ግለሰብ ነው። በከፍተኛ የወንጀል ድርጊቶች ላይ በመሳተፍ ፣ በማእከላዊ ታፍነው የሚሔዱ ታሳሪዎችን በመግለፍና በመደብደብ ፣ የተሳተፈና በዚህም ድርጊቱ በሕወሓት አመራሮች የፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ድረስ የደረሰ አረመኔ ነው። ግርማ ካሳ በዛሬው ፍንዳታ በደረሰበት ቦታ ላይ የሚገኘውን የፖሊስ መኪና እንዲቃጠልና መረጃ እንዲጠፋ አድርጓል ተብሎ ተወንጅሏል። ይህ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል ቀድሞ ከፍተኛ ጥርጣሪዎች ከፖሊስ መኮንኖች ቢቀርብለትም ስልጣኑን መከታ አድርጎ መረጃውን ማጣጣሉንና ሃሳቡን ያቀረቡትን አባሎቹን በቦታው እንዳይመደቡ ማድረጉን የኮሚሽኑ መኮንኖች ጠቁመዋል።

ፍንዳታው እንዲካሔድና ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መቀመጫ ለመቅረብ ይረዳ ዘንድ በፖሊስ መኪና ብቻ መጠቀም ስለሚቻል ይህን የፖሊስ መኪኖች ጥቃት አድራሾቹ እንዲጠቀሙበት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ ፈቃድ ሰጥቷል። በዚህም መሰረት የፖሊስ ላንድ ክሩዘሩ የሚችለውን ያሕል ሔዶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢያ ቦታ ላይ ቦምቡን ቢያፈነዱትም ወደ መድረኩ ከድምጽ ውጪ ምንም አደጋ አልደረሰም ። አላማቸው የነበረው ተቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ፍንዳታው ቢደርስ ኖሮ ባለስልጣናት መድረኩ ላይ አነጣጥረው የነበሩ ስናይፐሮች በግርግር ጠቅላይ ሚኒስትሩንና ምክትላቸውን የመግደል ኢላማ አድርገው ነበር። ይህ ሁላ ሲሆን ከስር ከስር ለምርመራ ያመቻሉ የሚባሉ መረጃዎችን ሁሉ እንዲያተፉና መኪናውንም እንዲያቃትሉ ግርማ ካሳ ቀጥተኛ ትእዛዝ መስጠቱን የበታች መኮንኖቹ ይናገራሉ ።

የአ/አ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽነር ኮማንደር ግርማ ካሳ በ1999 ዓ.ም ከምርጫ ዘጠና ሰባት ጋር በተያያዘ ለ35 ቀናት ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ታስሬ የደረሰብኝ ጭካኔ የተሞላበት ድብድብ ያስታውሰኛል። እኔ ምንሊክ ሳልሳዊ በዚህ ምድር ላይ እንደ ግርማ ካሳ ጨካኝ አውሬ መኖሩን እጠራጠራለሁ።

በወቅቱ ከመኖሪያ ቤቴ ወደ 6 ኪሎ ዩኒቪርሲቲ እየሄድኩ እያለሁ ከጠዋቱ 1 ሰዓት ላይ አራት ደህንነቶች በሁለት ቁጥር መኪና አፍነው ወደ ማዕከላዊ ተወሰድኩ። እዛ እንደ ደረስኩ አንድ መደበኛው ፖሊስ በሁከት እና ብጥብጥ ማነሳሳት ወንጀል መከሰሴን ጠቅሶ የእምነት ክህደት ቃል እንስጥ አደረገኝ። በዕለቱ ከ64 በላይ ሰዎች ከአአ ከተማ ታፍነው ማዕከላዊ ታስረው ነበር። ከምሽቱ 12 ሰዓት ሲሆን ግርማ ካሳና መድህኔ የሚባሉ ሰው አራጆች ለምርመራ ትፈልጋለህ ብለው ጠርተው ወሰዱኝ። ከዛ እጄን በካቴና አስረው የግድግዳ ኮለን አስደግፈው ምርመራ ማድረግ ጀመሩ። የማይመለከትኝ ጉዳይ ዙሪ ሲጠይቁኝ አላቅም አይመለከተኝም የሚል መልስ ሰጠኋቸው። በዚህ የተናደዱት ግርማ ካሳና መድህኔ ከቀኝና ከግራ በቦክስ አጣደፉኝ።

ከሁሉም በላይ የጎዳኝ ግርማ ካሳ ባለ በሌለ ኃይሉ ራሴን ከግድግዳው ኮለን ጋር በማጋጨት ያደረሰብኝ ጉዳት ነው። በወቅቱ በአፍና በአፍንጫዬ ደም እንደ ውሃ ሲፈስ አረመኔው ግርማ ባልዲ አምጥቶ ደሜን መደቀኑን አስታውሳለሁ። የዚያን ጊዜ የደረሰብኝ ጉዳት እስከ ዛሬ ያመኛል። እኔ ዕድለኛ በመሆኔ ህመም ቢሰማኝም በሕይወት አለሁ። አብረውኝ ታስረው ከነበሩ ግለሰቦች ውስጥ ብሎ እንደሆን ሰልፈኛው የሚባል ወጣት አቶ ታደለ የተባሉ የ60 ዓመት አዛውንት አረመኔው ግርማና ግብር አበሮቹ ባደረሱባቸው ድብደባ ከእስር ከተፈቱ በኋላ ሕይወታቸው አልፏል። ግርማ ካሳን ባሰብኩ ቁጥር የስንት ንፁሃንን ደም እንደፈሰሰ አስታውሳለሁ። በወቅቱ የቅንጅትን አመራሮች በሙሉ ሳይለንሰር በተገጠመለት ሽጉጥ መልቀም እየቻልን፤ መለስ ዜናዊ ምርጫ ምርጫ እያለ ዕድሜ ስጣቸው በማለት አምርሮ ሲናገር ሰምቼዋለሁ። ለግርማ ካሳ ሰው መግደል የዘወትር ተግባር እንጂ ወንጀል አይደለም። ( ምንሊክ ሳልሳዊ)

Filed in: Amharic