ግድ የለም አብይን እንመነው!!!  (ሀብታሙ አያሌው)

ግድ የለም አብይን እንመነው!!!

 ሀብታሙ አያሌው
በኢሬቻ በአል በኦነግ ባንዲራ የተሽቆጠቆጠችው ኢትዮጵያ በታሪኳ ሁሉ በጥምቀት ስትለብሰው የነበረው ሰንደቅ ዓላም ተገፍፏል።  አብይ ጥሩ እያሻገረን ነው።  ግድ የለም አባቶቻችን ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክሰው ያከበሩት ሰንደቅ ዓላማ ይረገጥ አብይ ለኢትዮጵያ ችግኝ ውሃ ስለሚያጠጣ ችግር የለም።
ግድ የለም ለውጡ እንዳይደናቀፍ የነጀዋር ትዕዛዝ እንዳይጣስ እኛ ዝም እንበል ኢትዮጵያ ትውደም።  ግድ የለም  አብይን እናምነዋለን  ኢትዮጵያ ቆዳዋ ተገፍፎ እንዲህ ሚጥሚጣ ቢነሰነስባትም እሱ እስካለ አያማትም።  ግድ የለም መቶ ፐርሰንት እንመነው።

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.