>

"የኢትዮጵያ ህዝብ መከራችንን ይመልከትልን!" (ቤታቸው በግፈኞች ፈርሶ ጎዳና ላይ የወደቁ ወገኖች)

“የኢትዮጵያ ህዝብ መከራችንን ይመልከትልን!”

ቤታቸው በግፈኞች ፈርሶ ጎዳና ላይ የወደቁ ወገኖች
ባልደራስ_አዲስ አበባ
.

.”ሰዉ እየተመረጠ ኮንዶሚኒዮም ቤት በሚሰጥባት ሀገር..”እኛ ምትክ ቤት ሳናገኝ ለምን ጎዳና ላይ ትጥሉናላችሁ” በማለት የጠየቁ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በታከለ ኡማ ፖሊስ ተደበደቡ።
 
..በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 በቀድሞ ስሙ ቀበሌ 15 በመባል የሚታወቀው ከሜጋ የኪነ-ጥበብ ማዕከል በስተጀርባ የሚገኙ ኗሪዎችን ትላንት ሰኔ 21/2012 ዓ.ም ለሊት በህገወጡ ከንቲባ ታከለ ኡማ የፖሊስ ሰራዊት ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጺመባቸው ገለጹ። በአካባቢው ለረጅም አመታት የቆዩ ነዋሪዎች ለሰዎች ኮንዶሚኒዬም ቤት እየተሰጠ ባለበት ወቅት እኛ ምትክ ቤት ሳይሰጠን መኖሪያ ቤታችን አፍርሰን ምን ላይ እንውደቅ ሲሉ የጠይቁ ወገኖች ይህን በማስመልከት ከንቲባዉ ይመጣል እሱን አነጋግሩ በማለት ወደ አንድ አካባቢ ካሰባሰቡን በኃላ በለሌት በርካታ ፖሊስ በማምጣት ድብደባ ተፈጽሞብናል ሲሉ ነዋሪዎቹ አቤቱታቸውን ለባልደራስ ተናግረዋል።
በአሁኑ ሰዓት ህጻናት የያዙ እናቶች ጎዳና ላይ እንደተበተኑ ባልደራስ በቦታው በመገኘት አረጋግጧል።  በአሳዛኝ ለቅሶ የሚናገሩት ነዋሪዎቾ የት እንሂድ? ሀገር አጣን ለኛ የሚቆረቆር ጠያቂ ወገን አጣን! ግራ ገባን በዚህ የወረርሽኝ ወቅት ያለ መጠልያ ተነፍገን  ቤታችን ፈርሶ መንገድ ላይ ወድቀናል እባካችሁ ድረሱልን በማለት በምሬት ተናግረዋል።
አንድ የአካባቢው ነዋሪ በኮየ ፈጬ እና በቦሌ ቡልቡላ ለተለያዩ ግለሰቦች ቤት እየተሰጣቸው እኛ በተወለድንበት ከተማ ያለ ሰብሳቢ መቅረታችን አሳዝኖናል ብለዋል።
አንዲት ልጅ የያዘኝ እናት ስሜት በሚነካ መልኩ በለቅሶ ሲገልጹ ብዙዎችን አሳዝናል። የኢትዮጵያ ህዝብ መከራችንን ይመልከትልን ያሉት የቀበሌ 15 ነዋሪዎች ስለፍትህ ያነባሉ።
በመጨረሻም በቦታዉ የተገኙ የባልደራስ አመራሮች የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ እስክንድር ነጋ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት እንደሚታገሉ ተናግረው። የከተማ አስተዳደር በየጊዜዉ በዜጎች ላይ የሚፈጽመው ውንብድና ለማስቆም በሰላማዊ መንገድ የተግባር እርምጃ በመውሰድ ይህን እንደሚያስቆመው በመናገር የአካባቢው ነዋሪ በትህግስት እንዲጠበቅ በማጽናናት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ሙሉ የቪዲዮ ምስል ይጠብቁ።
Filed in: Amharic