>
5:13 pm - Wednesday April 18, 0035

የአብይ አህመድ ኢትዮጵያ....!!! (ሀብታሙ አያሌው)

የአብይ አህመድ ኢትዮጵያ….!!!

ሀብታሙ አያሌው

 

የጠሚዶ አብይ ታሪክ በሙሉ በአማራ ደም  የተፃፈ ነው!
 
* በስልጣን ዘመናቸው ይህንን ያህል ቁጥር ያለው የአማራ ብሔር ተወላጅ ኢትዮጵያውያንን ተገደሉ ተብሎ የሚነገርላቸው ታሪክ ነው ያላቸው!
* የዶክተር አብይ ስርዓት እና ነባሩ አማራ ጠሉ ስርዓት የሚያከትመው አማራ ወጣት ንቅናቄና በሌሎች ትብብር ነው!
 
እስካልተነቃነቅህ ድረስ ሞትህ ይቀጥላል። ቁጥሩን መመስገብም የአንተ ስራ ነው!!
የዛሬው የጠቅላይ ሚንስትሩ የውጭ ጉዳይ አማካሪ አቶ ሌንጮ ባቲ፣ ከመቤተመንግስቱ ጀርባ ቆመው የፖለቲካውን ሂሳብ የሚሰሩት ሌንጮ ለታ እና ዶ/ር ዲማ ነጋዖ’ን የመሳሰሉት ኃይሎች ይመሩት የነበረው ኦነግ  በ1983
ዓ/ም  በበደኖ ፣ በአርባ ጉጉ … የአማራ ተወላጆችን እየመረጠ ህፃናት እና ሴቶችን ከነነፍሳቸው ገደል ከከተተ፣ አባወራዎችን እያረደ ከጣለ በኋላ በህወሓት በካልቾ ተመትቶ ኤርትራ በረሃ (አሬና)  ማሽላ ቆራጭ ሆኖ 27 ዓመት ያስቆጠረ  ደካማ ድርጅት እንደነበረ ይታወቃል።
ኦነግ እንደ ድርጅት መቆም አቅቶት 8 ቦታ ተበታትኖ መሪዎቹ ከአቶ ዳውድ ኢብሳ በቀር አውሮፓና አሜሪካ ተሰደው ሲኖሩ ተራው ወታደር እግሩ በመራው ተበታትኖ መሄጃ አጥተው የቀሩት ጥቂቶች   እዛው ኤርትራ በረሃ ማሽላ ቆራጭ ሆነው ኑሯቸውን ይገፉ ነበር።
እነዚህ ከተበታተነው ኦነግ ተርፈው የሻዕቢያ ጀነራሎችን የማሽላ ማሳ ሲንከባከቡ የኖሩ ቡድኖች በዛሬው ጠቅላይ ሚንስትር በትላንቱ የኢንሳ መሪ ኮለኔል አብይ አህመድ የመረጃ እና የገንዘብ ድጋፍ ይደረግላቸው እንደነበረ ይታወቃል።  (አብይ አህመድ ከመንግስት ስልጣን በስተጀርባ ይህንን ማድረጉን እንደ አገር ክህደት ሳይሆን እንደ ጀብድ ማውራቱም አይዘነጋም)
በብዙ መስዋዕትነት የውጡ አብዮት ገፍቶ ሲመጣ እራሱን በስውር ያዘጋጅ የነበረው አብይ አህመድ የብአዴን የፖለቲካ ድኩማን ኃይሎችን ተጠቅሞ የምኒልክን ቤተመንግሥት ተቆጣጠረ።  ወዲያውም በተጠና ስልት ከለማ መገርሳ ጋር ተናብቦ እራሱን የኢትዮጵያ አዳኝ አድርጎ አቀረበ።
አብይ አህመድ በፊትለፊት ህዝብ የሚፈልገውን በተመረጡ ቃላቶች ተናግሮ እያማለለ  የስልጣን ስጋት የሚላቸውን ጠራርጎ ለማጥፋት ብዙ ጊዜ አልወሰደበትም።  ህወሓት ቀድሞ በኢህአዴግ መዋቅር በተሰራው ወንጀል ተለይቶ ስለተኮነነ  ከመሐል ፖለቲካው ለመግፋት አልተቸገረም።  ወዲያውም ፊቱን ወደሌላው አዙሮ ለስልጣን ያበቃውን ብአዴንን ጃርት እንደበላው ዱባ በታተነው።
ደቡብ ክልንን እንዲያፈርስ ለአባዱላ የሰጠው ተልዕኮ ፈጣን ውጤት አምጥቶ ደቡብ ተበታተነ።  አባዱላ ደቡብን የመበታተን ስራው ሲጠናቀቅ በአንድ በኩል የባህልና የመሬት ወረራውን እያጣደፈ በሌላ በኩል ፊቱን ተረኛውን ሶማሌ ክልልን ወደማፈራረስ ተሸጋግሯል።
አብይ አህመድ ኤርትራ በረሃ ማሽላ ማሳ ውስጥ የነበሩትን በወቅቱ በሚስጥር ይረዳቸው የነበሩትን  ቡድኖች በለውጥ ስም ወደ አገር ውስጥ ካስገባ በኋላ ነፃ ቀጠና ፈጥሮ እንዲደራጁ አደረገ።  ኦነግ ህፃናትን መልምሎ ሲያሰለጥን ፤  ከ19 በላይ ባንኮችን ሲዘርፍ፣ የዘር ማፅዳት ወንጀል ሲፈፅም፣ አብይ አህመድ  አዲስ አበባ ከተማ የእስክንድ ነጋ ባልደራስ ላይ “ግልፅ ጦርነት” እንገባለን እያለ ሲፎክር ነበር።
ደሴ ሄዶ  የአማራ ክልል ልዩ ኃይልና ሚሊሻ መዋቅሩ እንዲፈርስ በይፋ ከተናገረ  ተልዕኮውን ለሚያስፈፅሙ የብአዴን ኃይሎች መመሪያ ከሰጡ በኋላ በኦሮሚያ 3 ዙሩ የልዩ ኃይል ሰራዊት አስመረቀ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በመከራ ተፈትና እንድትጠፋ በአብይ መንግስት ተፈርዶባት መከራዋን እያየች ነው።
አብይ በተግባር ኢትዮጵያን አፍርሶ ኦሮሙማን እየገነባ በአንደበቱ ኢትዮጵያ ትቅደም ማለቱን ቀጥሏል።
ኢትዮጵያን በተግባር መቀመቅ እየከተታት ነው። እነዚህ በፎቶ የምታያቸው ህፃናት በአፍሪካ አገራት ጫካውስጥ እንዳይመስሉህ በእኛዋ ኢትዮጵያ በኦሮሚያ እየሆነ ያለው የምታየው ነው።
በህወሓት ዘመን እንኳን ህፃናት መልምለህ አሰልጥነህ ምሽግ ቆፍረህ ልትንቀሳቀስ የኢትዮጵያን ድንበር ልትረግጥ ቀርቶ በጎረቤት አገር ስታልፍም የአንዳርጋቸው ፅጌ እጣ እንዳይደርስህ ተጠንቅቀህ ነው።  ህወሓት አንባገነን ነው ነገር ግን በመንግስትነት ዘመኑ  የተደራጁ አማፂዎች   ንፁሐንን እያረዱ በአገር ውስጥ ጦር ካምፕ ከፍተው ህፃናትን ለማሰልጠን መሞከር ግን  እንኳን በእውን በህልምም አይሞከርም ነበር።
                          … ይቀጥላል
የቴሌግራም ቻናል  
የሀብታሙ አያሌው እይታዎች
—————
የዩቱዩብ  ቻናል  
የሀብታሙ አያሌው እይታዎች 
Habtamu Ayalew 
 
የሀብታሙ አያሌው እይታዎች 
Habtamu Ayalew 
Filed in: Amharic