>
5:15 pm - Monday May 1, 0750

"ይሕ ፍፁም ከሩዋንዳው ኢንተርሐምዌ የወጣቶች አደረጃጀትና ተግባር ጋር የሚመሳሰል ተግባር ነው!" (ዶክተር ዳንኤል በቀለ...) 

“ይሕ ፍፁም ከሩዋንዳው ኢንተርሐምዌ የወጣቶች አደረጃጀትና ተግባር ጋር የሚመሳሰል ተግባር ነው!”

..(ዶክተር ዳንኤል በቀለ ለፋና ከሰጡት ቃለ-ምልልስ የተወሰደ ነው)
.
ትሕነግ በማይካድራ ማንነትን መሠረት አድርጎ ከ600 በላይ ንፁሓንን ጨፍጭፏል 
* የማይካድራው  ፍጅት የመርሃ-ግብሩ ቅደም ተከተልና ቅድመ ዝግጅት  
.
* ጭፍጨፋው ……., ዝግጅት ተደርጎበታል ።
* ጥቃቱ ተግባራዊ የሆነው በታጣቂዎች ጥበቃና ከለላ እየተደረገለት ይንቀሳቀስ ከነበረው  ” ሳምሪ ” እየተባለ የሚጠራው የአካባቢው የወጣቶች አደረጃጀት ነው ።
* ወጣቶቹ …. በአካባቢውም የሚታወቁ ናቸው ።
* ጥቃቱንም ሲፈፅሙ በሚሊሻና በፖሊስ እየታጀቡና ከቤት ቤት እየዞሩ ነው ።
* ጭፍጨፋውና ግድያው በዱላ ፣ በስለት ፣ በጩቤ ፣ በፋስ ፣ በመጥረቢያ ግማሾቹ ደግሞ በገመድ አንገታቸው እየታነቀ ነው ።
* ቡድኑ በተለይም የአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ትኩረት አድርጎ ነው ጭፍጨፋውን ያከናወነው ።
* ቀደም ሲል ሰዎች ከቤታቸው እንዳይወጡ መመሪያ ተላልፎላቸውል ።
* ገዳይ ወጣቶቹ በከተማው መውጫና መግቢያ ቦታዎች ከአካባቢው ሚሊሻና ፖሊስ ጋ በመቀናጀት ኬላ አቋቁመው ሰው እንዳይገባና እንዳይወጣ ሲቆጣጠሩ የነበር ።
* ሰዎች ማንነታቸውን ለመለየት በመታወቂያቸው ጭምር የመለየት ስራ ተከናውኗል ።
* የሱዳን ሲም ካርድ ያላቸው ሰዎች ስም ካርዳቸው ተወስዶ እንዲሰባበር ተደርጓል ፣
* ከዚህ በሗላ ጥቅምት 30 መንገድ የመዝጋቱ ሒደት በከፍተኛ ደረጃ ተጠናቀቀ ።
* በተጠቀሰው ቀን 5 ሰአት ላይ ተጨማሪ የማንነት ማጣራት ተግባር ተከናወነ ።
* ከሰአት በሗላ 9 ሰአት ላይ የመጀመሪያው ጥቃት ተፈፀመ ።
* ቀጥሎ ለሊቱን ሙሉ ሲካሄድ አነጋ ።
* ሊያመልጡ የሞከሩ በጥይት ተመተው ተገለዋል ።
* በጥቃቱ ሊስት ውስጥ የሌሉ ግን ደግሞ ተጠቂዎችን ለማዳን የሞከሩ  የግድያው ሰለባ ሆነዋል ።
* ጠዋት ጥቃቱን ሲፈፅሙ ያነጉት ቡድኖች (ሳምሪዎች )  ፣ ሚሊሻዎችና ፖሊሶች ከተማውን ለቀው ወጥተዋል ።
Filed in: Amharic