>

ንጉሳችን ኢሳያስ ሆይ! እባክህ ስማን! ልደቱ ይታከም! (ተስፍሽ ነኝ ከቶሮንቶ)

ንጉሳችን ኢሳያስ ሆይ! እባክህ ስማን! ልደቱ ይታከም!

ተስፍሽ ነኝ ከቶሮንቶ

.*… እንደተለመደው ዛሬም አቶ #ልደቱ አያሌው ለሕክምና እንዳይወጡ ተከልክለዋል የዛሬውን ለየት የሚያደርገው ፓስፖርታቸውን እና ሌሎች ማስረጃዎቻቸውን መቀማታቸው ነው!
 
 
ባሻዬ! “ንጉስ አይከሰስም” ፤ ሰማይ አይታረስም ሲባል ሰምታችሁ ሊሆን ይችላል ትክክል ናችሁ ንጉሰ ነገስት “ኢሳያስ አፎርቄ” የማይከሰሰው ፤ የማይወቀሰው ፤ ንጉሳችን ዛሬ ‘በታላቋ ቅድስት’ ሀገር ኢትዮጵያ ላይ ታላቁ ክንዳቸውን አሳርፈው ያሻቸውን ያደርጋሉ ፤ ማንም ተሳስተዋል ልክ አይደሉም የሚላቸው ጠፍቶ ሀገራችንን በፍቅር እያስተዳደሩ ይገኛሉ።
.******
በገዛ ሀገራቸው ብኩርናቸውን የሸጡት አብይ ፤ ደመቀ ፤ ባጫ ፤ እና እርዝራዥ የደህንነት ሀላፊ ሰራተኞች ዛሬ ላይ ከንጉስ ኢሳያስ ትህዛዝ ውጪ ምንም ማድረግ የማይችሉ በድኖች ሆነዋል! ወታደር ማዝመት ቢሆን ፤ ማሰር ፤ መፍታት ፤ ማገት ቢሆን መግደል የሚያስፈፅሙት የኢሱን ትዛዝ ብቻ ነው። ይሄን ስናገር የሆነ በሬ ወለደ ጥላቻ እንዳይመስላችሁ።
.*****
አቶ ልደቱ አያሌው የኢትዮጵያ ዜግነት ያለው ፖለቲከኛ በገዛ አንደበቱ ከዚህ ቀደም ስለ ኢሳያስ ሲናገር እንዲህ ብሎ ነበር”ኢትዮጵያ ውስጥ የኢትዮጵያ ጠላት የሚባል ካለ በአለም ላይ ቁጥር1 ሰው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ናቸው” እንዲህ ብሎ የተናገረው ልደቱ ከዚህን ቀን ጀምሮ በኢሳያስ ጥርስ ውስጥ ገብቷል። ይህ ትክክለኛ ንግግር ኢሱን አበሳጭቶታል።
.******
ከመንግስት ባለስልጣን ደግሞ ቃል በቃል ልደቱን ለምን አታርፍም እኔ ላንተ ብዬ ነው ኢሳያስ ይገልሀል ተብሎ ተነግሮታል። ይሄንንም ልደቱ ቃል በቃል በሚዲያ ተናግሯል። ይህው እውነት ቀኑን ጠብቆ ልደቱ በገዛ ሀገሩ በኢሳያስ ደህንነቶች ፤ በኢሳያስ ትህዛዝ እየተሰቃየ ይገኛል ህግ ነፃ ብሎ የለቀቀው ልደቱ ፤ መንግስት በደብዳቤ የለቀቀው ልደቱ ታዲያ ማን እያሰቃየው ነው?
.*****
ወዱ ኢሳያሳችን የኛ መሪ ፤ የኛ አለቃ ፤ እባክህ ዛሬ እርህራሄ አድርገህለት ልደቱ አያሌው ወደ ውጪ ወጥቶ እንዲታከም ፍቀድለት። አንተ ምርጥ የአለማችን መሪ እኮ ነህ። ኢሱ አንተ እኮ ኤርትራን ያሳደግህ ፤ በኢኮኖሚ ያበለፀግህ ፤ ወጣቱን በፍቅር የተንከባከብክ ፤ የሀገርህን ዜጎች በሀብት ያትረፈረፍክ መሪ እኛንም ልክ እንደ ኤርትራ ስለምታሳድገን እናመሰግናለን።
.*****
ለዘመናት ለኛ ለኢትዮጵያውያን መልካም ነገር የምታስብልን ፤ ለኛ እድገት እንቅልፍ የሌለህ ልዩ ፍቅር ለሁሉም ኢዮጵያዊ ያለህ ፤ ከውድ ሀገር ኤርትራ በላይ ለኛ ለኢትዮጵያውያን የምትሳሳልን የምትጨነቅልን ፤ ለኛ ብለህ ጦርነት ያደረክልን ኢሱ ፤ በቃ ለኛ ያለህን ፍቅር ፤ እድገት፤ የሰላም እቅድ ሁሉ ደርሶናል እናመሰግናለን። አሁን ግን ልደቱን ብቻ ልቀቅልን ይታከም።
.*****
ስለሰማህኝ አመሰግናለሁ! 
Filed in: Amharic