>

በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የሚንቀሳቀሱ የአማራ ፖለቲከኞችን ለመብላት የሸረበው ሴራ  ....!!!

በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የሚንቀሳቀሱ የአማራ ፖለቲከኞችን ለመብላት የሸረበው ሴራ  ….!!!
አቻምየለህ ታምሩ

በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ “6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማደናቀፍ በህቡዕ ተደራጅተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖችን እኩይ ሴራ ማክሸፉን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ” በሚል ትናንት  በሰበር ዘና ባቀረበው  ጨቅላዊ ድራማውና የአማራ ፖለቲከኞችን ለመብላት በሸረበው ሴራ እጅ ከፈንጅ ያዝሁት ብሎ ከነገረን አስረጂዎች አንዱ አሜሪካን አገር ተፈጥሯል ባለው የአማራ ህቡዕ አደረጃጀት ውስጥ አባል ናቸው ያላቸው ፕሮፌሰር አበራ መሸሻ የሚባሉ ሰው ሕግና ስርዓትን ጣሳ ባለው መልክና በስውር አዘጋጁት ያለው 85 ገፆች ያሉት ሕገወጥ የተባለ አዲስ ረቂቅ ሕገ መንግሥት ነው።
ሲጀመር ማንም ሰው ያሻውን መጻፍና ረቂቅ ሕገ መንግሥት ነው ብሎ የማቅረብ መብት አለው።  ሲቀጥል ዐቢይ አሕመድ በደረሰው ጨቅላዊ ድራማ በደኅንነት መስሪያ ቤቱ እጅ ተፈንጂ እንደተያዘ በሰበር ዜና የተነገረው በፕሮፌሰር አበራ መሸሻ እንደተዘጋጀ  የተነገረለት “ሕገ ወጥ ረቂቅ ሕገ መንግሥት” ፕሮፌሰሩ በ1988 ዓ.ም. ያሳተሙትና ላለፉት 25 ዓመታት በአማዞን አማካኝነት ሲሸጡ የከረሙት መለስተኛ መጽሐፍ ነው። ምን ይሄ ብቻ! ፕሮፌሰሩ ራሳቸው በሁለት ዓመታት በፊት ከመታሰቢያ ቀጸላ ጋር በኢሳት ቴሌቭዥን  ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደነገሩን ይህን ያዘጋጁትን ሕገ መንግሥት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለአቶ ለማ መገርሳና በአሜሪካን የኢትዮጵያ አምባሳደር ለሆነው ሰው በእጅ መስጠታቸውን ነግረውናል።
ልብ በሉ! በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ በትናንትናው እለት ባስነገረው ሰበር ዜና  በደኅንነት መስሪያ ቤቱ እልህ አስጨራሽ “የክትትል ሂደት” የተገኘ ሚስጥር አድርጎ ያቀረበውና  በሕቡዕ ተፈጠረ  ከተባለው የአማራ አደረጃጀት እጅ ከፈንጅ ተያዘ የተባለው ረቂቅ ሕገ መንግሥት  ፕሮፌሰር አበራ መሸሻ ላለፉት 25 ዓመታት በአማዞን ላይ ሲሸጡ  የከረሙትንና ዛሬም ማንም ሊያነበው የፈለገ ሰው ከአማዞን በማዘዝ ሊገዛው የሚችለውን “Democratic Constitution for Ethiopia”  የተሰኘ መለስተኛ መጽሐፍና ለዐቢይ አሕመድ ለራሱ ፕሮፈሰሩ የሰጠቱን ተቂቅ ሕገ መንግሥት ነው። ዐቢይ እንዲህ አይነት ቀሽም ድራማ ሊሰራ የቻለው ሁሉን ሰው እንደቄሮ የነገሩትን ሳያረጋግጥ ተቀብሎ የሚሮጥ አድርጎ ስለሚንቀው ነው። ድንቄም!
በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ የሚንቀሳቀሱ የአማራ ፖለቲከኞችን ለመብላት በሸረበው ሴራው  ያወናከረው ሌላው ድራማ የወለጋውን ኦሮሞ ፕሮፌሰር አበራ መሸሻን በድራማው የፈጠረው አሜሪካን አገር የሚገኝ የአማራ ሕዝዕ አደረጃጀት አባል አድርጎ ማቅረቡ ነው። ሰውዬውኮ በበላኤ ሰብዕ ዘመን የተደመሩ፤ ቀደም ሲልም በጁኔይዲ ሳዶ ትዕዛዝ የኢንቨስትመንት መሬት “ኦሮምያ” ውስጥ ተሰጥቷቸው የነበሩ የደምቢዶሎ ሰው የኦቦ መሸሻ ዋቄ ልጅ ናቸውኮ።
በላኤ ሰብዕ በአስቂኝ ድራማው በደኅነት መስሪያ ቤቱ እስህ አስጨራሽ ክትትል የተገኘ አደረጃጀት አድርጎ በሰበር ዜና ያቀረበው ሌላው ነገር በZOOM የተደረገን ፐብሊክ ስብሰባ ነው። ZOOMንም የሕቡዕ አደረጃጀቱ  በሚስጥር ሲጠቀምበት እጅ ከፈንጅ የተያዘ ልዩ መሳሪያ አድርጎ አቅርቦታል።  በደኅንነት መስሪያ ቤቱ  እልህ አስጨራሽ ክትትል የተያዙት ሕገ ወጥ ቡድኑ ታጠቃቸው የተባሉት መሳሪያዎች ደግሞ አንድ አሮጌ ሽጉጥ፣ አሮጌ ቢላዋና ያረጁ የእጅ ስልኮች ናቸው። የአማራ ልጆችን ተከታትሎ አንድ አሮጌ ሽጉጥ፣ አሮጌ ቢላዋና ያረጁ የእጅ ስልኮችን የያዘው የደኅንነት መስሪያ ቤት የኦሮሞ ልጆች  ከመጋዘን የወጣ አዲስ ጠመንጃ ድራጉኖቭ አነጣጥሮ ተኳሽ ጠመንጃ [Dragunov Sniper Rifle] የሚባል ሲሆን ሩስያ ሰራሽና ባለመነጽርና የረጅም ርቀት ጠመንጃ ሲታጠቁ፣ ሸዋሮቢትንና አጣዬን ሙሉ በሙሊ ሲያወድሙ፣ ሴቶችን ሲያፍኑና እልቆ ቢስ ንጹሐንን በጅምላ ሲፈጁ አይዝም። ይህ የሚያሳየው በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ የደሕንነት መስሪያ ቤቱን ያደራጀው እነማንንን ለመተታተል እንደሆነ ግልጽ ነው።
ስለ አዲስ አበባ ዝም አንልም ማለትም ሕገ ወጥ መሆኑ፤ “አማራን መጨፍጨፍ ይቁም!” እና  “በሕፃናት ደም ምርጫ የለም!” መባሉም አደገኛ ቅስቀሳዎች መሆናቸውን በላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ በሰበር ዜና ባስነገረው ድራማው ነግሮናል።
ሲጠቃለል የበላኤ ሰብዕ ዐቢይ አሕመድ የትናንትናው ድራማ የሚያሳየው ነገር ቢኖር ብሔራዊ ደኅንነትና ፌዴራል ፖሊስ በሚባሉት መስሪያ ቤቶች በኩል የአዲስ አበባ አማራዎችን የመብላት ስራው መጀመሩን ነው። ይህ ማለት እስካሁን ድረስ ክልሎች በሚባሉት የሚኖረው በማንነቱ  ሲገደል፣ ሲታፈን፣ ንብረቱ ሲቃጠልና ሲፈናቀል የኖረው አማራ አጣ ፈንታ አዲስ አበባ ውስጥ በሚኖረው አማራ ላይም በይፋ መጀመሩን የትናንትናው የበላኤ ሰብዕ ድራማ ቁልጭ አድርጎ አሳይቶናል። በትናንትናው እለት እንኳን በርካታ የአዲስ አበባ የአማራ ወጣቶችና እና የአማራ ባለሃብቶች በብሔራዊ ደኅንነት መስሪያ ቤቱ ተይዘዋል።
በሰበር ዜናው  ተያዙ ተብለው የታዩት ግን አብዛኛዎቹ  በደኅንነት መስሪያ ቤቱ የተዘጋጁ የደህንነት አባላት ናቸው። በላኤ ሰብዕ ይህንን የማናውቅ ይመስለዋል።  ከእነዚህ ጋር አብረው የተያዙትና ባለሀብት ተብለው የቀረቡት አንዱ ናደው ዘውዱ (በአዲስ አበባ የየረር ኮንስትራክሽን ባለቤት ነው) ይገኝበታል። አንድ የሪፐፕሊካን ጋርድ አማራም አብሮ ተይዟል።
በጣም የሚገርመው ደግሞ ተይዘው ገና በፌዴራል ፖሊስ  ተብዮው በኩል የወንጀል ምርመራ ሳይደረግላቸውና ቃል ሳይቀበሉ ቀድሞ የተዘጋጀውን የዐቢይ ድራማ ስክሪፕት በኢቢሲ በኩል ሰበር ዜና ተብሎ መነገሩ ነው። በዚህ ሳምንት በአዲስ አበባ ብዙ የአማራዎች እስር እንደሚቀጥል ከውስጥ ምንጮቻችን ተረጋግጧል። በላኤ ሰብዕና አገዛዙ የአዲስ አበባን አማራ ለመሰልቀጥ ይህንን ሁሉ እያደረገ  አብዛኛው የአዲስ አበባ አማራ ግን  ከመደራጀትና ለኅልውናው ከመታገል  “የአራዳ ልጅ ሀገር እንጂ ዘር የለውም፤ ዘር ለ ገበሬ ነው” እያለ  ራሱን ሲያታልል ይውላል።
ከታች የታተመው በደኅንነት መስሪያ ቤቱ ክትትል ተያዘ የተባለው ፕሮፈሰር አበራ መሸሻ  ከ25 ዓመታት በፊት ያሳተሙትና ዛሬም ድረስ በአማዞን ላይ በመሸጥ የሚገኘው “ረቂቅ ሕገ መንግሥት ነው” ሽፋን ነው። የሚከተለውን ሊንክ በመጫን በአማዞን ላይ ታገኙታላችሁ!
Filed in: Amharic