>

" እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! " ባልደራስ

” እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! “

ባልደራስ

 

የማህበራዊ ድረ-ገፅ ዘመቻ ጥሪ!
ከጥቅምት አንድ እስከ ሦስት !
    በግፍ እስር ላይ የሚገኙት የባልዳራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ አስቴር ስዩም እና ወሪ/ት አስካለ ደምሌ ከ1 ዓመት በላይ ያለ ጥፋታቸው ፤ ለዲሞክራሲ ፣ ለፍትሕ እና ለእኩልነት በመወገናቸው እና የፖለቲካ አመለካከታቸው እንደ ወንጀል ተቆጥሮ በግፍ ከታሰሩ ከአንድ አመት በላይ ሆኗል።
   በዚህ ጊዜ ውስጥ አንዳች የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ አልቀረበባቸውም ። አመት ሙሉ ሲጓተት የከረመው የምስክሮች አሰማም ሂደት ከታችኛው ፍ/ቤት እስከ ሰበር ጠቅላይ ፍ/ቤት ተመሳሳይ ውሳኔ ቢሰጥም ምስክሮችም በግልጽ ችሎች መቅረብ እንዳማይችሉ መንግሥታዊው ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ በተደጋጋሚ ገልጿል ። በዚህ መሐል ንጹሃን ያለ ብይን ከአንድ አመት በላይ በግፍ እስር እንዲቆዩ ተደርገው እየተጉላሉ ይገኛሉ ።
   በእስር ቤት ውስጥ ከሌሎች እስረኞች በተለየ በአቶ እስክንድር ነጋ እና በአቶ ስንታየሁ ቸኮል ላይ የወህኒ ቤቱ አያያዝ እጅግ በጣም የከፋ ሆኗል ። ይህንን አስከፊ የእስር ቤት አያያዝ አስመልክቶ ፍርድ ቤት እስረኞቹን አስመልክቶ
የቂሊንጦ ወህኒ ቤት አፋጣኝ ማስተካከያ እንዲያደርግ ያስተላለፋቸው ትዕዛዞች አንዳቸውም ተግባራዊ አልተደረጉም ። እነ እስክንድር ፖለቲካዊ መብቶቻቸውን በመንግስት በሃይል ተነጥቀዋል ፣ ሰብዓዊ መብቶቻቸው እየተጣሰ ይገኛል።
    ይህም በመሆኑ ፦ በሰላማዊ የነፃነት ታጋዮች ላይ እየደረሰ ያለው መንግስታዊ በደል ፣ የፍትሕ እጦት፣ የሰብዓዊ መብት ገፈፋ እና ያለ ጥፋታቸው መታሰራቸው አግባብ አለመሆኑን በመግለጽ በአስቸኳይ ከግፍ እስር እንዲለቀቅ የሚጠይቅ ሁሉን አቀፍና አሳታፊ የሆነ  ” እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! ” በሚል መሪ ቃል የሦስት ቀን የበይነብ ዘመቻ ይደረጋል፡፡
   ዘመቻው ሰኞ ከጥቅምት 1 እስከ ረብዕ ጥቅምት 3/2013  ዓ.ም የሚደረግ ሲሆን፤ የፖለቲካ እስረኞች እነ እስክንድር ጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የፀረ ሽብርና የሕገ መንግሥት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ይቀርባሉ። መረጃዎች በመለዋወጥ ፣ ለኢትዮጵያውያን፣ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰቡና ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በማሳወቅ ላይ ያተኩራል፡፡
   የበይነ መርብ ዘመቻው በፌስ ቡክ፣ በቲውተር ፣ በኢንስታግራም፣ በአገር ውስጥና በውጭ ባሉ ሬዲዬ፣ ቴሌቪዥን ፣ በምስል በድምፅ በፎቶና በካርቶን ስዕሎች፣ በቪዲዬዎች ይደገፋል። እነኚህ መልዕክት አስተላላፊ ዘዴዎች በመዓከል ደረጃ የሚዘጋጁ እንዳሉ ሆነው ፤ የዘመቻውን ዋና ዓላማ ከግብ የሚያደርስ የትኛውንም አመራጭ ዘዴ ማንም ሰው በራሱ ፈጠራ መጠቀም ይቻላል ።
  በዚህም መሠረት ፤ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች ፣ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች ፣ የማህበረሰብ አንቂዎች ፣ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት  በሚካሄደው የበይነ መርብ ዘመቻ እንደተሳተፉ እና የሚመለከታችሁን ተግባራት እንድታከናውኑ በአክብሮት እንጠይቃለን።
 ” እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! “
Filed in: Amharic