የእስክንድርን ምግባር ማድነቅን ከአብይ አምልኮ ጋር ለምታመሳስሉ ውታፍ ነቃዮች …!!!
ድንበሩ ደግነቱ

ፀጋዬ አቡነ ጴጥሮስ ለቅድስት ኢትዮጵያ የከፈሉትን የሰማዕትነት ዋጋ እንደአንድ ኢትዮጵያዊ ለውለታ ክብር መስጠቱ እንጅ አቡነ ጴጥሮስን ማምለኩ አልነበረም። አሁንም እንደዛ ጀብራሬ እስክንድርን ጉዋደኞችህ የትና የት ሹመት አግኝተዋል፣ አንተ ዝም ብለህ ፌስታል ይዘህ በቺስትነት ትንከራተታለህ እያሉ እንደጀብራሬው የሚሳለቁበት የዓቢይ ካድሬዎች በዝተዋል። እነዚህ ባለጌዎች እንደጀብራራው የሰማዕታት ውለታ ላይ እንደሸኑ እቆጥረዋለሁ። እንደ እስክንድር ለኢትዮጵያ ታላቅነት ክብርና ለዜጎችዋ ልዕልና መስዋዕትነት መክፈል ባልበቃ እንኩዋን እንዚህን ባለጌዎች በፌቡ መፋጠጥ ግን አያቅተኝም። የእስክንድርን ምግባር ሳዳንቅ ግለሰብን እያመለኩ ሳይሆን እንደ ፀጋዬ ለቅድስት ኢትዮጵያ የተከፈለን መስዋዕትነት እያከበርኩ መሆኔ ይታወቅልኝ።