>
5:37 pm - Sunday January 21, 8024

በመተከል ከጉምዝ ታጣቂዎች ጋር በተደረገ ተኩስ ሁለት የአማራ ልዩ ሃይል አባላት ተሰው

በመተከል ከጉምዝ ታጣቂዎች ጋር በተደረገ ተኩስ ሁለት የአማራ ልዩ ሃይል አባላት ተሰው
 አንድ ሌላ የአማራ ታጣቂም ተሰውቷል
ጌጥዬ ያለው
በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ፤ ማንቡክ፤ ጉልባክ ቀበሌ ከኦነግ-ሸኔ እና ሕወሓት ጋር ጥምረት እንደፈጠረ ከሚነገርለት የጉምዝ አማጺ ቡድን ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ሁለት የአማራ ልዩ ሃይል አባላት ተሰውተዋል። ያልተገባ መስዋዕትነት እንዲከፍልና አደረጃጀቱ እንዲፈስ እየተደረገ እንደሆነ ከሚነገርለት ልዩ ሃይል፤ አስራሦስቱ መቁሰላቸውንም ከስፍራው የመረጃ ምንጮች አረጋግጠዋል። ከአሸባሪዎቹ አጋር የጉምዝ አማጺ በኩል ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ በርካታ ታጣቂዎች ተገድለዋል። በሀገር መከላከያ ሰራዊት ባለቤትነት ብቻ እንደሚያዝ የሚታወቀውን ሞርታር የአማራ ልዩ ሃይል ከጉምዝ ታጣቂ ማርኳል።
በተያያዘ ዜና ባለፈ ባለፈው ሰኔ 19 ቀን 2014 ዓ.ም. ከማል ጋሹ የተባለ ሌላ አማራ ታጣቂ በጉምዝ አማፅያን ጋር ሲፋለም በማንቡክ ከተማ አቅራቢያ ተሰውቷል። ወጣቱ በአካባቢው በርካቶችን በማሰልጠን ይታወቃል።
ከማል ጋሹ
Filed in: Amharic