>

ጦርነት እገጥማለሁ ካለ ጋር ያለው አማራጭ መግጠም ብቻ ነው (መስፍን አረጋ )

ጦርነት እገጥማለሁ ካለ ጋር ያለው አማራጭ መግጠም ብቻ ነው

መስፍን አረጋ

 


 

መከራን እንደመጋፈጥ፣ ፈርቶ የሚፈረጥጥ

ይጠብቀዋል ቀውጥ፣ ይበልጥ የሚሰቀጥጥ፡፡

ጣጥሎ በመሮጥ፣ እየመሰለው የሚያመልጥ

ይገባል ብሎ ቀጥ፣ ከሳት ወጥቶ ረመጥ፡፡

 

ጭራቅ አሕመድ ጦርነት እገጥማለሁ ብሎ የዛተው ከእስክንድር ጋር ብቻ ሳይሆን እስክንድርን ከመሰሉ ሁሉ ጋር ነው፡፡  በጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ግዛት ውስጥ ኦነጋዊ ያልሆነ ሁሉ ጊዜው ደርሶ በሜንጫ ተቆራርጦ በጭራቁ እስከሚበላ ድረስ መኖር የሚችለው የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ ጉዞ ለይስሙላ ቢቃወምም በተግባር ግን የማያደናቅፍ እስከሆነ ድረስ ብቻ ነው፡፡  የጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ጉዞ ደግሞ መዳረሻው አማራን ድምማጡን ማጥፋት ነው፡፡  

ስለዚህም ጭራቅ አሕመድ ለአማራ ሕዝብ የሰጠው ምርጫ ሁለትና ሁለት ብቻ ነው፡፡  አንደኛው ምርጫ (ምርጫ ከተባለ) ተራ በተራ እየታረደ በጭራቁ ተበልቶ እስከሚያልቅ ድረስ የጭራቁን ጭራቃዊ አገዛዝ አሜን ብሎ ተቀብሎ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ ነው፡፡  ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ የጭራቁን ጦርነት ግጠሙኝ ገዲር (challenge) በጸጋ ተቀብሎ ከጭራቁ ጋር ሞት ሽረት በመፋለም ወይ ጭራቁን መቀጥቀጥ አለያም በጭራቁ መሰልቀጥ ነው፡፡ 

አንደኛው ምርጫ ተዋርዶ ኑሮ ተዋርዶ የመሞት ምርጫ ስለሆነ የቱሪናፋ ምርጫ ነው፡፡  ሁለተኛው ምርጫ ደግሞ ተከብሮ የመኖር ወይም በክብር የመሞት ምርጫ ስለሆነ ያርበኛ ምርጫ ነው፡፡

ስለዚህም ተዋርዶ ኑሮ ተዋርዶ መሞትን የማይመርጥ አማራ ሁሉ አርበኛ ሁኖ፣ ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ ብሎ፣ የነ በላይ ዘለቀን ጦርና ጋሻ አንስቶ፣ የሞት ሽረት ትግል ለማድረግ ዱርቤቴ ማለት አለበት፡፡  ባትዋጋ እንኳን በል እንገፍ እንገፍ፣ ያባትህ ጋሻ ቱኻኑ ይርገፍ፡፡   

በደኖና ዝዋይ፣ ቡራዩና ቄለም

ኦነግ ያፈሰሰው ያማራ ጥቁር ደም

ውሻ ልሶት ቀርቶ እንደሌለው ወንድም

እንዳይፋረድህ በወዲያኛው ዓለም፣

አማራ ጦር አንሳ ኦሮሙማን ግጠም

በሂወትህ ቆርጠህ ሞት ሽረት ተፋለም፡፡

ደም በደም ካልጠራ ስለሚሆን መርገም

ባፈሰሰው ደም ልክ አፍስስ የኦነግ ደም

በደንብ አርገህ ቅጣው እንዳያስብ መድገም፡፡

 Email; mesfin.arega@gmail.com

 

Filed in: Amharic