>

ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል የመጀመሪያና የመጨረሻ ግቦች! 

ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል የመጀመሪያና የመጨረሻ ግቦች

መስፍን አረጋ

ያማራ ሕዝብ ሕልውናውን ለማስጠበቅ ሲል ያልሞት ባይ ተጋዳይ የሞት ሽረት ትግል እያደረገ፣ በትግሉም ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለና ታላላቅ ድሎችን እየተጎናጸፈ ይገኛል።  ስለዚህም ይህ ከፍተኛ መስዋዕትነት እየተከፈለበት ያለው ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል የመጀመርያና የመጨርሻ ግቦቹ  ምንድን ናቸው ብሎ መጠየቅ የግድ ነው።

ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል የመጀመርያ ግብ መሆን ያለበት የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግስት ገርስሶ ጭራቅ አሕመድንና ግብራበሮቹን (በተለይም ደግሞ የአብን፣ የኢዜማና እና የብአዴን ግብራበሮቹን) ማስተማሪያ በሚሆን መንገድ አይቀጡ ቅጣት መቅጣት ነው።  የጭራቅ አሕመድን ኦነጋዊ መንግስት ሳይገረስስ የሚጠናቀቅ ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል ግቡን ሳይመታ እንደ ከሸፈ (ባጭር እንደተቀጨ) ይቆጠራል፡፡  

ስለዚህም ከጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ መንግስት ጋር እደረደራለሁ ወይም እሸማገላለሁ የሚል ፋኖም ሆነ ሌላ ማናቸውም ቡድን፣ ያማራን ሕዝባዊ ትግል ባጭር የሚያስቀጭ ያማራ ሕዝብ ቀንደኛ የሕልውና ጠላት መሆኑ ታውቆ፣ እሱ ራሱ ባፋጣኝና ባስፈላጊው መንገድ ባጭር መቀጨት አለበት፡፡  እደግመዋለሁ ከጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ መንግስት ጋር እደራደራለሁ የሚል ፋኖ ነኝ ባይ ወይም ደግሞ አሸማግላለሁ የሚል ሽማግሌ ነኝ ባይ ካለ፣ ማንም ይሁን ማን ያማራ ሕዝብ አጣዳፊ ጠላት መሆኑ ታውቆ፣ ባጣዳፊ ተዘምቶበት ባጣዳፊ መወገድ አለበት።  

በመጀመርያ ደረጃ ድርድር የሚደረገው ከሰው ጋር ነው።  ጭራቅ አሕመድ ደግሞ አቶ ታየ ደንድአ በትክክል እንደገለፀው ያማራ ደም እየጠጣ የሰከረ ጭራቅ እንጅ ሰው አይደለም።  ለጭራቅ ምድሐኒቱ ደግሞ በተገኘው መሳርያ ወሳኝ ብልቱን በርቀሶ ጨርቅ ማድረግ ነው። 

ጭራቅ አሕመድን ጨርቅ አድርጎ ኦነጋዊ መንግስቱን መገርሰስና የጭራቁን ግበራበሮች (ደመቀ መኮንን፣ ተመስገን ጡሩነህ፣ ብናልፍ አንዷለም፣ አበባው ታደሰ ወዘተ.) አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ዘላለማዊ መቀጣጫ ማደርግ ግን ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል የመጀመርያ ግብ እንጅ የመጨረሻ ግብ አይደለም፡፡  ያማራ ሕዝብ ሕልውና ለዘላለም የሚረጋገጠው፣ ዘላለማዊ ጠላቶቹ ወያኔና ኦነግ ሙተው ተቀብረው ለዘላለም ሲወገዱ ብቻ ነው።  

ስለዚህም ያማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል የመጨረሻ ግብ ወያኔና ኦነግን እንደ ድርጅት ለዘላለም ማጥፋት ነው።  ወያኔንና ኦነግን በናዚነት ወይም ፋሽስትነት ፈርጆ፣ የነሱን ሐሳብ በሚያራምድ ማናቸውም ግለሰበ ወይም ቡድን ላይ የማያዳግም ወሳኝ እርምጃ መውሰድ ነው።  ያማራ ልጆች ደግሞ በወያኔና በኦነገ ዘመን ባማራ ሕዝብ ላይ የተፈፀመውን ፍጅት በትምህርት ቤቶችና በቤተመዝክሮች እየተማሩ እንዲያድጉና፣ ወያኔ ወይም ኦነግ ብቅ ሲል ባዩ ቁጥር በሲቃ ተነሳስተው እንዲያንቁት ማድረግ ነው።       

መለስ ዜናዊ፣ ጭራቅ አሕመድና መሰሎቻቸው የበሽታ ምልክቶች እንጅ በሽቶች አይደሉም።  ወያኔና ኦነግ የሚባሉት ዘር ጨፍጫፊ፣ አገር አጥፊ ወረርሽኞች ልክ እንደ ፈንጣጣ ወረረሽኝ ከምድረገፅ ከጠፉ፣ በወረርሽኞቹ የሚያዙ መለስ ዜናዊንና ጭራቅ አሕመድን የመሰሉ የወረርሽኝ በሽተኞች አይኖሩም፡፡ ነገር ከፍንጩ፣ ውሃ ከምንጩ።   

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

Filed in: Amharic