>

የንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ሁለት የፖሊስ መኮንኖችንና የወረዳ የወያኔ ስራ ኣስፈጻሚ ተገደሉ። ፖሊስ ወደ ሕዝቡ ሲተኩስ ነበር

(ምንሊክ ሳልሳዊ)

Jawar Mohammed 29062016 News on LaftoJawar Mohammed 29062016 News on Lafto.1jpgተጨማሪ መረጃ በፖሊስና በነዋሪዎች መካከል በተነሳዉ ግጭት 17 ፖሊሶች መሞታቸዉን ነዋሪዎቹ ገለጹ።‪#‎BBN‬
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ወያኔ ሕዝቡን ወንጅሎ ከቀየው ለማፈናቀል እና ለማሰር እያደረገ ያለው ሴራ የሰዎች ሕይወት ቀጥፏል፥ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የህዝብን ቤቶች ለማፍረስ እቅድ በተመለከተ የክፍለ ከተማው አስተዳደር ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር ሲወያይ የነበረበትን ስብሰባ ከደህንነት ቢሮ የተላኩ የወያኔ ኣባላት በፈጠሩት ግርግር ሁለት የፖሊስ መኮንኖችን እና በክፍለ ከተማው የወረዳ አንድ ስራ አስፈፃሚ አባል ህይወትን አጠፉ። ፖሊስ ወደ ሕዝቡ ሲተኩስ ነበር።

የደህንነት ኣባላቱ ወንጀሉን ከሰሩ በኋላ በመጡበት መኪና ተሰውረዋል። የደህንነት ሃይሎቹ በፈጠሩት ግርግር ምክንያት የወያኔ መስተዳደር ኣባላት ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ይህ ሁሉ ችግር ሕዝብን ለመወንጀል የተደረገ መሆኑ የኣከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ። እስካሁን በኣከባቢው የሞቱ ሰላማዊ ሰዎች ቁጥር ኣልታወቀም።
ላፍቶ፦ ተጨማሪ መረጃ
በአዲስ አበባ አካባቢ በላፍቶ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ቀርሳ ኮቱማ በሚባለዉ አካባቢ በፖሊስና በነዋሪዎች መካከል በተነሳዉ ግጭት 17 ፖሊሶች መሞታቸዉን ነዋሪዎቹ ለቢቢኤን ገለጹ።በፖሊሶችና የቀበሌ አመራሮች በአካባቢዉ ያሉትን ቤቶች ለማፍረስ የመብራት ቆጣሪዎችን ለመንቀል ሲሞክሩ በተነሳዉ ግጭት ነዋሪዎቹ የፖሊሶቹን መሳሪያ በመቀማት፣በዱላና በድንጋይ በተከፈተ ጥቃት ነዉ ፖሊሶቹ የሞቱት።

ግጭቱን ተከትሎ የጦር መሳሪያን የታጠቁ የፌዴራል ፖሊሶች ወደ አካባቢዉ በመግባት ነዋሪዉን እየደበደቡ በጭነት መኪና እያፈሱ ወዳልታወቀ ቦታ እየወሰዱ መሆኑን ቢቢኤን ለማወቅ ችሏል። ህጻናትና እናቶች ያለቤት አባወራ ሜዳ ላይ እንደተጣሉና ለአደጋ እንደተጋለጹ ነዋሪዎቹ ያስረዳሉ።ጿሚዎች ማፍጠሪያ ምግብና ቦታ እንደሌላቸዉ ገልጸዋል። እራሳቸዉን ከፌዴራል ፖሊስ ጥቃት ለማዳን የሚሸሹ የቤት አባወራዎች በየጫካዉ ዉስጥ መቀመጣቸዉን፣ ምንገዶች ሁሉ መዘጋታቸዉን ነዋሪዎቹ ለቢቢኤን ገልጸዋል።ከነዋሪዎቹ ለመረዳት እንደተቻለዉ ቢያንስ አንድ የቀበሌ አመራር ሞቷል።‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

#‎Ethiopia‬ ‪#‎AddisAbaba‬ ‪#‎StateTerrorism‬

Filed in: Amharic